lunedì

የዚህ ድህረገጽ ዓላማ *** ለኢትዮጵያዊያን መቀራረቢያ ድልድይ መሆን፣ *** በየጊዜው የሚደነግገውን የእምግሬሽን ሕግ በአጭሩ ማቅረብ፣ *** ከጣሊያን ሕትመቶች ላይ ኢትዮጵያ ነክ ዜናዎችን መርጦ ማቅረብ፣ *** ስነፅሁፍ፣ ቃለ መጠይቅ፣ የታሪክ ዘገባ፣… ማቅረብ፣ *** በጣሊያን ህግ፣ ደንብና የዜጎች እኩልነት መርህ ላይ በመመሥረት ሕጋዊ የሆነ ማህበራዊ ተቋም እንዲኖረን፣ *** መሰረታዊ የሆኑ ማህበራዊ መብቶችን ለማወቅ፣ *** የመወያያ መድረክ በመሆን ራሳችንን ለሰው ሀገር ኑሮ ለማዘጋጀት፣ *** ልምድን በማካፈልና በመቅሰም የራስ ላይ እምነት እንዲኖረን፣ *** ወጣቶች የኪነጥበብ፣ የስፖርት... ችሎታቸውን እንዲያዳብሩና ለአደባባይ እንዲበቁ ማገዝና ማበረታታት፣ *** በውጪው ኑሮአችን የመቻቻል፣ የመፈላለግና የልብ ውህደት እንዲኖር ጥረት ማድረግ፣ *** ማዝናኛ ቪዲዮዎች፣ ቀልዶችንና ሙዚቃዎችን መለገስ፣ *** የጣሊያንኛ ቋንቋ ችግርን ማስወገድ ይቻል ዘንድ ፅሑፎችን በአማርኛ ተርጉሞ ማቅረብ፣ *** አንባቢያን አስተያየቶቻቸውን ማቅረብ እንዲሁም ጠይቀው መረዳት እንዲችሉ ማድረግ፣ *** የኢትዮጵያን ባሕላዊ የኑሮ ስልት ለማሳወቅ፣ *** የጣሊያንን ባህል፣ ልምድ፣ ወግና ኑሮ በበለጠ ለማወቅ፣ *** በኢትዮጵያ ሳይንስና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የሚስፋፉበትን ዘዴዎች መቀየስ፣ *** የጋራ ችግሮቻችንን በሕጋዊ መንገድ ለመፍታት ማስቻል፣ *** ውጪ ከሚኖሩ ወገኖች ጋር ሃሳብ ለመለዋወጥ፣ ወዘተ ...


በትውልድ ኢትዮጵያዊቷ አዜብ በቦሎኛው ምርጫ በእጩነት ቀረበች


ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ
24 - 04 - 2011

……....እንደፈረንጆች አቆጣጠር በሚቀጥለው 15 እና 16 maggio 2011 የቦሎኛ ከተማ ነዋሪዎች አስተዳዳሪዎቻቸውን እንደገና ለመምረጥ በሚያደርጉት ዝግጅት የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወዳዳሪዎች እራሳቸውን ለህብረተሰቡ በማስተዋወቅ ለከተማዋ እድገትና ደህንነት ምን ማድረግ እንዳቀዱ አላማቸውን በተለያዩ የዜና ማሰራጫ ዘዴዎች በመግለፅ ለሕዝቡም ቃል በመግባት ላይ ይገኛሉ:: ካለፉት የምርጫ ልምዶች መረዳት እንደሚቻለው ተመራጮች ሁሉም ቃል ገቡ ማለት ተግባራዊ አደረጉት ማለት አይደለም፣ እንዲያውም ብዙውን ጊዜ ምርጫው ካበቃ በኋላ በፊት ቃል ገብተው እንደነበርም አያስታውሱትም::
……....የብዙዎቹ ተወዳዳሪዎች ወቅታዊ መፈክር "የውጭ አገር ዜጋ ብዛትና የወንጀለኛው ቁጥር መጨመር"፣ ከውጭ አገር ዜጋ ወረራ እናድንሃለን እና የመሳሰሉት ናቸው፣ ከእውነት የራቁ መልእክቶችን በማሰራጨት በነዋሪው ላይ የፍርሃት መንፈስ እንዲሰፍን ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛሉ::
……....ይህን የጥላቻና የዘረኝነት ጥቃት እንዴት መቋቋም ይቻላል? መልሱ የማያሻም ይሆናል የራስን መብት ማስከበር የሚቻለው ሌላውን በመለመንና በመለማመጥ፣ ወይንም ከዳር ቆሞ በመመልከት ሳይሆን በየወቅቱ በሚደረጉት ሕዝባዊ ምርጫዎች በመካፈል እኔን ወክሎ መልእክቴን ያስተላልፋል፣ ብሶቴን ለሚመለከተው የበላይ አካል ያሰማልኛል ብለው ያመኑበትን ሰው በመምረጥ ነው::


ባጭሩ አዜብ ማናት?

……....አዜብ የ25 አመት እድሜ ያላት ወጣት ስትሆን በትውልድዋ ኢትዮጵያዊት ዜግነትዋ ጣሊያናዊ ነው:: በትምህርትዋም በማሕበራዊ ኑሮ የዩኒቨርስቲ ምሩቅ ስትሆን በተማረችው የትምህርት ዘርፍ በመሥራት ላይ ትገኛለች:: እንዳጫወተችኝ በዚህ ምርጫም ለመወዳደር የገፋፋት በቦሎኛ ከተማ በሚኖሩት ወገኖችዋና በውጭ አገር ዜጎች ላይ እየተደጋገመ በመካሄድ ላይ ያለውን የዘረኝነት ጥቃት ለማስቀረት ነው::
በመካፈል አዜብን እንምረጥ
ደህና ሁኑ ::

Azeb Lucà Trombetta candidata al Comune di Bologna

…….... Esiste nelle periferie e nel centro di questa città. Esiste sui campi di basket, nelle piazze, nei parchi e nelle scuole.
E' un potente esercito.
Sono i giovani ai quali nessuno riconosce il loro diritto ad Essere. Un potente esercito che si muove con le proprie rabbie e le proprie frustrazioni, perché il diritto a scegliere gli è stato negato.
Mi sento parte di questo esercito: figlia della rossa Etiopia da 25 anni e da 20 cittadina italiana. Mi chiamo Azeb Lucà Trombetta e sono laureata in mediazione culturale e da 3 anni mi occupo della rappresentazione mediatica dei giovani italiani di origine straniera e dei loro incroci identitaria.
Vi invito a fare una passeggiata per le vie; vi invito a parlare con i ragazzi di piazza dell'Unità, con quelli che popolano piazza Maggiore, e in tutti i quartieri della città.
Lì c'è l'energia che cerco, che serve e che ha bisogno di ascolto.
Vorrei partire dai contorni, dai luoghi di tutti; partire dalle "mosse dell'anima", e dalle azioni quotidiane.
Vorrei iniziare a parlare di cittadinanza come sentire e come vissuto. Che sia fatta di reciprocità, di dialogo reale e di condivisione e non di forme (spesso folkloristiche) di integrazione.
Vorrei parlare di cittadinanza come reale progetto di civiltà, che valga per Tutti.
Ecco perchè mi candido.

www.crossingtv.it
azeb.lucatrombetta@gmail.com




Da Addis Abeba a Lampedusa

la storia di Dagmawi Ymer

(4 Aprile 2011)

……...."Cinque anni fa non me lo sarei mai immaginato". Dagmawi Ymer è etiope, è arrivato in Italia da clandestino via mare nel 2006 ed è sbarcato a Lampedusa. "Sull'isola sono rimasto una settimana in un centro di accoglienza vicino all'aeroporto. L'unica cosa che ricordo bene sono gli aerei dei turisti" racconta Dagmawi ai microfoni di SkyTG24. Oggi ha trovato il modo di far sentire la sua voce attraverso il cinema e i documentari.

……....Quando Dagmawi è scappato dall'Etiopia era il periodo delle manifestazioni contro le elezioni presidenziali del 2005 accusate di esser state truccate. "Invece di morire per niente o di essere arrestato, ho deciso di associarmi ad un gruppo di ragazzi che avevano pensato di partire per la Libia. Ma nessuno prevede niente, nessuno sa a cosa sta andando incontro". Una volta arrivati in Libia, Dagmawi e i suoi compagni di fuga sono stati arrestati dalla polizia libica e deportati in un container nella prigione di Cufra in attesa dell' "espulsione". "Lì c'è un meccanismo per cui la polizia ti cede ad intermediari", dichiara Dag. E' il cosiddetto sistema dei poliziotti, una consuetudine piuttosto semplice e redditizia che costringe gli immigrati a pagare una somma per poter essere portati in una delle città portuali libiche e da li essere nuovamente venduti ad altri intermediari che li caricano su dei barconi per fare la traversate. Un giro d'affari di 20 milioni di euro: dopo il petrolio lo sfruttamento dei clandestini è una voce molto florida per l'economia libica. "Una volta che arrivi in Italia, da dove puoi chiamare la tua famiglia e poter di dire di stare bene e essere consapevole che comunque non sarai maltrattato, è un sollievo".

……....Dagmawi una volta arrivato in Italia in soli due mesi è riuscito ad ottenere lo status di protezione umanitaria, e si è trasferito a Roma dove ha imparato l'italiano e fatto un corso di video partecipato e da quel momento ha deciso di iniziare a raccontare attraverso le immagini la sua storia: "Mi dichiaro un documentarista per caso. Questo mi ha dato la possibilità di dare voce a chi a differenza di me, non ce l'ha fatta a scappare".
……....
CINQUE ANNI FA È SCAPPATO DALL'ETIOPIA E PASSANDO PER LA LIBIA HA RAGGIUNTO L'ISOLA SICILIANA. ORA VIVE A ROMA E FA IL DOCUMENTARISTA, PER CERCARE DI RACCONTARE CON LE IMMAGINI CIÒ CHE I SUOI OCCHI HANNO VISTO. LA TESTIMONIANZA


"Europa, paghi il tuo egoismo"

Parla il regista etiope Dagmawy Yimer, autore di documentari sull'immigrazione

Intervista di Giulia Cerino

(25 febbraio 2011)

……...."L'Occidente ha stretto accordi con i peggiori dittatori del mondo, per avere il loro petrolio o il loro gas. E adesso si capisce che era una visione miope, che la real politik non può ignorare i diritti umani fondamentali". ……....La Libia è a ferro e fuoco, i rivoltosi si avvicinano a Tripoli e stanno per scontrarsi con gli uomini fedeli a Gheddafi. Mentre nel Paese migliaia di migranti da altri paesi africani sono allo sbando, terrorizzati da quello che sta avvenendo e alla disperata ricerca di una barca che li porti in Europa. Di tutto questo parliamo con Dagmawi Yimer, etiope, regista (insieme ad Andrea Segre e Riccardo Biadene) del film-documentario "Come un uomo sulla terra" (2008) e ora all'opera su il nuovo video-racconto "Benvenuti in Italia", cinque storie d'integrazione conquistata o negata. Dag è nato ad Addis Abeba 34 anni fa. Proprio passando attraverso la Libia, nel 2005, è sbarcato a Lampedusa. Ora parla un italiano perfetto. …….... ……....Dag, secondo te che cosa sta succedendo in Libia? «Uomini e donne rivendicano i diritti dei cittadini di uno Stato democratico, e quindi rifiutano il modello del rais onnipotente. Gheddafi cadrà perché la rivolta di questi giorni non è guidata da "movimenti separatisti che minacciano l'unità nazionale" come ha detto Seif al-Islam, figlio del dittatore. Quelli in piazza sono persone comuni. Il governo cadrà». La maggior parte dei libici però non ha mai conosciuto altro sistema politico che quello instaurato da Gheddafi... «Gheddafi potrebbe riuscire a mantenere il potere solo ad ovest. In quel caso si arriverebbe alla spartizione del Paese in due. Ma alla fine tutto dipenderà dalle reazioni dei capi tribali che detengono il controllo del petrolio». ……....E poi? ……....«Se dovesse compiersi anche la liberazione dell'ovest, allora arriveremmo alla transizione verso la democrazia. Ci vorrà tempo per abituarsi al cambiamento e alle regole democratiche. Di certo c'è che molti clandestini che ora sono in Italia tornerebbero nelle loro case con tutto ciò che hanno imparato e acquisito da voi. Con la Tunisia sta già succedendo. Avverrebbe anche per Libia». …….... ……....Bengasi festeggia la liberazione ma ci sono centinaia di morti in seguito alla repressione. Cosa deve fare l'Europa ……....«Gheddafi non è un interlocutore. L'Europa non avrebbe dovuto comunicare o fare affari. Mi sorprendo che non abbiano previsto, prima o poi, una rivolta del genere. Sono o non sono loro i big della diplomazia internazionale? Dovevano pensarci prima e da paesi democratici trovare una vera soluzione. In Libia c'è sempre stata la dittatura. Come pretendere che i clandestini vengano riportati indietro senza che vengano violati i loro diritti? Quello che l'Europa avrebbe dovuto fare era di creare le condizioni affinché gli africani arrivassero in Libia e fossero in grado di rimanere liberi. Avrebbero dovuto tutelare i diritti individuali dell'uomo, non lasciare che prevalesse il principio di sovranità nazionale i stati che non sono affidabili. Io, se ci fosse stata una situazione decente in Libia non avrei preso una barca verso Lampedusa. Non avrei affrontato il mare. Ma sarei rimasto lì dov'ero. Si tratta di affermare la libertà di fermarsi. Prendere un provvedimento del genere avrebbe reso inutile un accordo sull'immigrazione. I flussi si sarebbero ridotti, e soprattutto si potrebbe ora parlare di responsabilità reciproca».
……....Pur con qualche contorsione diplomatica, Obama ha mantenuto la promessa ed ha appoggiato i movimenti democratici. L'Europa ha condannato la repressione pronunciandosi in favore degli oppositori in rivolta. Soltanto l'Italia di Berlusconi ha tardato all'appuntamento.
……....«Se l'insurrezione libica affogherà nel sangue anche il governo italiano avrà la sua parte di responsabilità. Quello che sta succedendo è stato causato e incentivato dall'egoismo europeo che pur di mantenere in piedi gli accordi economici e gli affari su gas e petrolio, ha preferito sorvolare sulla questione dei diritti umani. Il supporto a Gheddafi è stato economico ma anche psicologico. L'Europa ha cioè spesso fatto credere al dittatore di poter chiudere un occhio sul regime a patto che filassero lisci i piani economici. Prendiamo la Cina. Non la vedi mai sostenere direttamente i governi dittatoriali ma economicamente c'è. In Africa è ormai quasi dappertutto. Mi stupisce che l'Europa non riesca a comportarsi così. Cos'ha che non va?




Dagmawi Yimer al Festival di Internazionale




……....Durante il Festival di Internazionale a Ferrara, la nostra Azeb Lucà Trombetta ha intervistato il filmaker Dagmawi Yimer dopo la proiezione del suo ultimo documentario “Soltanto il mare“.

Intervista di Azeb Lucà Trombetta riprese di Akio Takemoto montaggio di Silvia Storelli ringraziamo Dagmawi Yimer



"Soltanto il mare"


Regia, fotografia, suono: Dagmawi Yimer, Fabrizio Barraco, Giulio Cederna Montaggio: Fabrizio Barraco Coordinamento: ...... Musica: Nicola Alesini
 Formato: DVCAM Versione Originale: italiana Distribuzione: Lettera 27 Note di regia

……....Ci troviamo a Roma alla fine di maggio del 2009: un etiope sbarcato a Lampedusa, un trapanese che a Lampedusa ha vissuto felicemente per anni, e un romano che Lampedusa non l’aveva vista nemmeno con il binocolo. Lavoriamo insieme all’Archivio delle Memorie Migranti dell’associazione Asinitas, montiamo cortometraggi in un abbaino rosolato dal sole e di tanto in tanto pensiamo alle vacanze. L’ipotesi di andare tutti insieme a Lampedusa si impone quasi subito, all’inizio quasi per gioco, poi come un richiamo insistente, rilanciato ogni giorno dalle pagine dei quotidiani. L’Italia ha appena firmato l’accordo con la Libia, le notizie di nuovi arrivi si mescolano alle cronache dei primi “respingimenti”.

……....Partiamo senza un progetto preciso ma con due idee chiare: 1) guardare l’isola, e il fenomeno dell’incontro tra isolani e arrivanti, dalla prospettiva nuova di chi effettivamente sull’isola è appena sbarcato; 2) accogliere l’inderogabile volontà di Dag di non occupare il centro della narrazione, di non fare il “personaggio” - lo è già stato abbastanza nella vita e in altri film – per non rubare la scena all’isola e ai suoi personaggi. E’ assai più difficile, ma in fondo è questa la sfida: daremo il ruolo di protagonista al suo sguardo, alla sua capacità di mettere in scena l’isola con la videocamera. (E così è accaduto: il novanta per cento delle riprese montate, tutte quelle sull’isola, i suoi paesaggi, la corsa di Cocò, i momenti di vita, la processione, sono opera sua…).

……....Sbarchiamo a Lampedusa all’inizio di agosto, in pieno scirocco. Ci svegliamo alle cinque del mattino e riprendiamo dalle sei alle nove e mezza - prima che il sole bruci ogni cosa - o al tramonto. Non abbiamo un piano preordinato, luoghi, situazioni, persone, da raccontare; cerchiamo, “peschiamo”, piuttosto, videocamera e cavalletto in spalla, gli occhi e le orecchie ben aperte. In questo modo incontriamo Cocò, un signore distinto di una certa età che fa jogging ogni mattina all’alba sulla strada di Ponente. La camicia sudata appiccicata al petto, i pantaloni lunghi, il volto attempato contratto dalla fatica, rivelano che non è un turista. Lo seguiamo e lo filmiamo per giorni, senza mai fermarlo, senza chiedergli niente. La sua grintosa corsa nel nulla ci affascina, è una meravigliosa metafora dell’umano affannarsi sull’isola.

……....Ogni mattina ci svegliamo e andiamo a pesca di storie e di personaggi. In questo modo arrivano anche Pep Top, Zi Pasquale, Rizzitelli. Scopriamo che l’isola non è popolata solo da navigatori ma anche da insospettabili poeti: un maestro d’asce che fa cortometraggi, un pescatore-attore, un cantante. Scopriamo che a Lampedusa non c’è un ospedale e non nasce più nessuno da anni. Scopriamo che anche qui il mare si è ammalato e dà sempre meno pesci. Scopriamo che i migranti sono chiamati “turchi”. Così, decidiamo di ritornare una seconda volta, a settembre, per riprendere la processione della Madonna di Porto Salvo, cerimonia fondante dell’isola, e scopriamo che il corteo che unisce tutto il paese è guidato da un prete della Tanzania.

……....Giorno dopo giorno l’isola si apre e ci regala nuove storie, situazioni inaspettate, cortocircuiti. Al migrante fresco di sbarco l’isola era apparsa come l’avanguardia del benessere - con i suoi alberghi, le sue barche, i suoi turisti - alla nostra videocamera si svela ora piena di problemi; l’aveva immaginata come frontiera del progresso, la ritroviamo isolata dal mondo, con lo sguardo nostalgico rivolto al passato e una patina fresca di vernice già incrostata di salsedine.

……....Il momento più emozionante è l’incontro con l’equipaggio della 282, la motovedetta della guardia costiera che ha salvato Dag dal naufragio e da una morte certa. Siamo tutti così emozionati che portiamo a casa a stento qualche immagine buona… e il definitivo “grazie” a quest’isola che, proprio come accade ai migranti, paga lo scotto di un’informazione emergenziale e deformante.

……....In maniera naturale ci sembra stia accadendo quanto ci eravamo ripromessi di fare: inquadratura dopo inquadratura, la storia di Dag finisce confluire nella storia collettiva, stratificata e polifonica dell’isola; isola nella quale finisce per perdersi e ritrovarsi innanzitutto come autore, regista e persona, e non più soltanto come semplice “clandestino”, pass numero otto del quarto sbarco del 30 luglio 2006.

http://soltantoilmare.blogspot.com/p/note-di-regia.html





ማ ስ ታ ወ ቂ ያ

የአማርኛ ቋንቋ ትምሕርት በቦሎኛ ዩኒቨርስቲ

ክፍል ስድስት

ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ Feb 2011

……....ባለፉት አመታት በተከታታይ በቦሎኛ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ የነበረው የአማርኛ ቋንቋ ትምሕርት በዚህም በያዝነው የትምህርት አመት የሚቀጥል ስለሆነ በዚህ አጋጣሚ በመጠቀም በአዲስ ተመዝጋቢነት ትምህርቱን ለመጀመር ወይንም መጠነኛ የአማርኛ ችሎታቸውን ማሻሻል ለሚፈልጉ ሁሉ ትምህርቱ ያለምንም ክፍያ በነፃ የሚሰጥ መሆኑን እንገልፃለን::

ስለትምህርቱ ሰፊ ማብራሪያ ለማግኘት በሚቀጥለው ቁጥር መደወል ይቻላል Tel. 3395764139


የአማርኛ ቋንቋ ትምሕርት በቦሎኛ ዩኒቨርስቲ ይቀጥላል


ክፍል አምስት


ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ 15 02 2010


……....የአማርኛ ቋንቋ ትምሕርት ባለፉት አመታት በተከታታይ በቦሎኛ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ እንደቆየ ይታወሳል:: ይህንን የቋንቋ ትምሕርት መሰረት በማድረግ ብዙዎች ተማሪዎች; መምህራንና የተቋም የሙያ ባልደረባዎች አስፈላጊውን ምርምርና ጥናት በተገቢው መንገድ ለማካሄድ እድል አግኝተዋል ብሎ ለማለት ይቻላል:: ……....በዚህ በያዝነውም የትምሕርት አመት (anno accademico 2009/2010) ትምህርቱ በድጋሜ እንዲሰጥ ከብዙ ተማሪዎች ጥያቄ በመቅረቡ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በሳምንት ሁለት ጊዜ ማለትም ረቡዕና አርብ በሚከተለው አድራሻ መሰጠት ተጀምሮአል::

Dipartimento di Discipline Storiche Piazza San Giovanni in Monte 2 (sede del corso è in Via Centotrecento)

ኮርሱን በተመለከተ አስፈላጊውን ማብራሪያ ለማግኘት የሚከተሉትን የኮርሱ አስተባባሪዎች ያነጋግሩ::

Dr. Zeleke Eresso Goffe Coordinamento Interdistrettuale Sistemi Informativi Automatizzati di Bologna Tel. 3395764139 zeleke_eresso@yahoo.it Prof. Irma Taddia Dipartimento di Discipline Storiche Piazza San Giovanni in Monte 2 40124 Bologna Tel. +39 051 2097674 irma.taddia@unibo.it


የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በቦሎኛ ዩኒቨርስቲ


ክፍል ሁለት


ዶ/ር ዘለቀ እሬሶ


……… የኢትዮጵያን ዩኒቨርስቲዎች ከቦሎኛ ዩኒቨርስቲ ጋር ለማስተዋወቅና አልፎም የጋራ ስምምነት በመፈራረም አብሮ መሥራት እንዲችሉ ታቅዶ ካለፈው አመት ጀምሮ የተለያዩ የሥራ ፕሮጀክቶች ተዘርግተው በሥራ ላይ መዋል ጀምረዋል:: ……… ከፕሮጀችቶቹም አንዱ በቦሎኛ ዩኒቨርስቲ የአማርኛ ቋንቋ ትምህርትን በመጀመሪያ ደረጃ ለመምህራንና ለከፍተኛ ጥናት ምርምር ተማሪዎች ቀጥሎም የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ማስተማር ይገኝበታል:: ይህ በጣሊያን አገር ሲከሰት የመጀመሪያው ሲሆን ባለፈው አመት የትምህርት ዘመን በተሰጠው ትምህርት ላይ ብዙዎች በመካፈል አስደሳች ውጤት ሊገኝበት ተችሏል:: አብዛኞቹም በትምህርቱ ተካፋይ የነበሩት የዩኒቨርስቲ መምህራን እንደመሆናቸው መጠን በተለያዩ ሙያዎችም ኢትዮጵያ በመመላለስ ይሰሩ የነበሩ በመሆናቸው ትምህርቱን በሙሉ ፍላጎት ለመከታተል ከመቻላቸው ሌላ ሊደሰቱበትም እንደቻሉ በተደጋጋሚ ወቅት ተናግረዋል:: ……… በዚህ በያዝነውም የትምህርት ዘመን በድጋሜ ትምህርቱን ለመቀጠል በተስማማነው መሰረት ትምህርቱ በሚቀጥለው እ.ኤ.አ 20/02/2009 ስለሚጀመር ተካፋይ መሆን የሚፈልግ ሁሉ በሚቀጥለው አድራሻ ደውሎ በመጠየቅ መረዳት ይችላል::



LEZIONI DI AMHARICO PRESSO IL DIPARTMENTO DELLE DISCIPLINE STORICHE – UNIVERSITA’ DI BOLOGNA Dipartimento Discipline Storiche Storia Moderna e Contemporanea dell’Africa Piazza S. Giovanni in Monte, 2 - 40124 BolognaTel.+39 051 209 7600 Tel.+39 051 209 7700fax 051 209 7620 Per informazione rivolgersi: Prof. Irma Taddia – Coordinatrice Dr. Zeleke Eresso Goffe - Docente CISIA di Bologna Tel. 3395764139


የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በቦሎኛ ዩኒቨርስቲ


ክፍል አንድ



2007/2008 የትምህርት አመት


………በቅርቡ በቦሎኛ ዩኒቨርስቲ በቋንቋ ዲፓርትመንት ተዘጋጅቶና ተቀነባብሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በሳምንትን ሁለት ቀን ለዩኒቨርስቲ መምህራንና ለተማሪዎች በሰፊዉ መሰጠት ተጀምሮአል:: የፕሮግራሙ ዋና አላማ በቦሎኛና በአካባቢዋ ለሚገኙ የዩኒቨርስቲ መምህራን በተለይም በቋንቋዎች ጥናት መስክ በመሰማራት የቋንቋ ችሎታቸዉን ለማዳበር ለሚጥሩት ሁሉ ድጋፍ ይሆናል ተብሎ የተዘጋጀ ነዉ:: ……… ይህ ፕሮጀክት ከግብ ሊደርስ የቻለዉ ቀደም ሲል በቦሎኛ ዩኒቨርስቲና በጥቂት የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ መቀሌ ዩኒቨርስቲ፣ ጅማ ዩኒቨርስቲ፣ ወለጋ ዩኒቨርስቲና ደቡብ ዩኒቨርስቲ) መካከል ተደርጎ በነበረዉ የዩኒቨርስቲዎች ሳይንሳዊ የጋራ ስምምነት መሰረት ነዉ:: እኔም በዚሁ የጋራ ስምምነት በመካፈል ትምህርቱን ከሚሰጡት ምሁራን አንዱ በመሆን በኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎችና በቦሎኛ ዩኒቨርስቲ መካከል መልካም የሳይንስና የቴክኖሎጂ እድገትና ብልጽግና እንዲስፋፋ በማለት ለመነሻ ያህል የአማርኛ ቋንቋን ትምህርት ለመጀመሪያ ጊዜ በጣሊያን አገር በዩኒቨርስቲ ደረጃ ለማቅረብ ተሞክሮአል:: ……… ሰሞኑን የመቀሌ ዩኒቨርስቲ ልኡካን ቡድን በቦሎኛ ዩኒቨርስቲ የስራ ጉብኝቱን ፈጽሞ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሷል::




ዜና እረፍት

……....ጥሩነሽ: "እውነትም ጥሩ ነሽ"
……....ወ/ሮ ጥሩነሽ ደምሴ ከአባታቸው ከሻምበል ደምሴ በዳኔ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ በቀለች ወ/ሃዋርያት እ.አ.አ. በ01/07/1951 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ተወለዱ:: እድሜያቸው ለትምህርት እንደደረሰ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በእቴጌ መነን ትምህርት ቤት ካጠናቀቁ በኋላ ቀጥሎም በአዲስ አበባ የንግድ የትምህርት ዘርፍ በሆነው የኮሜርስ ኮሌጅ ትምህርታቸውን አጠናቀው በአካውንቲንግ ዲፕሎማ ተመርቀዋል:: ከዚህም በኋላ ለተወሰኑ አመታት አዲስ አበባ በሚገኘው የጀነራል ውድ እንዱስትሪ መሥሪያ ቤት ተቀጥረው በመሥራት አገልግሎታቸውን በብቃት ተወጥተዋል:: እ.አ.አ. በ 1977 ዓ.ም. ወደ ጣሊያን አገር በመምጣት ኑሮአቸውን በቦሎኛ ከተማ አድርገው በሥራ ሲተዳደሩ የኖሩና ለረጅም ጊዜ እስከመጨረሻ ቀናቸው ድረስ ከባለቤታቸው ከአቶ ጆቫኒ ቦርዮኒ ጋር በጋብቻ ተሳስረው ቆይተዋል:: ……....ወ/ሮ ጥሩነሽ በቦሎኛ ከተማ የሚገኘውን የኢትዮጵያውያን ባሕላዊ ማህበር ከመሰረቱት መሥራች ግለሰቦች የመጀመሪያዋ ሲሆኑ ከሥራ አስኪያጅ ኮሚቴ አባላት መካከልም ዋነኛዋ ሴት ከመሆናቸው ሌላ በወገኖቻቸው ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያፈሩ አስተዋይና አገር ወዳድ ሴት ናቸው:: ለሰው ልጅ በተለይም ለወገናቸው ከነበራቸው የጋለ ፍቅር በመነሳት የተቸገረን ሁሉ በመርዳት፣ ያዘነን በማፅናናት፣ የተጣላን በማስታረቅ ባጠቃላይ የወገኖቻቸውን ጭንቀት በማቅለል በበጎ አድራጊነት ወገናዊ የእርዳታ ድርሻቸውን ተወጥተዋል:: ……....ወ/ሮ ጥሩነሽ ትሁትነትን፣ ሀቀኝነትን፣ ሰው አክባሪነትን፣ አስተዋይነትን በኑሮአቸው የሕይወት መመሪያ በማድረግ የኖሩ እንደነበሩ የሚያውቁዋቸው ግለሰቦችና በተለይም የቅርብ ጓደኞቻቸው ሁሉ የሚመሰክሩት ነው:: ምንም እንኳን ወ/ሮ ጥሩነሽ ላለፉት አመታትና በያዝነው አመት በተለይም በዚህ በመጨረሻዎቹ ወራት አካባቢ በተለያዩ የቦሎኛ ከተማ ሆስፒታሎች በሕክምና ሲረዱ ቢቆዩም ባደረባቸው የፀና ህመም ምክንያት እ.አ.አ. በ 23.09.2010 በሃምሳ ዘጠኝ አመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል::
……...."መልካም ስም ከመቃብር በላይ ይውላል" እንዲሉ ወ/ሮ ጥሩነሽ በበጎ ሥነምግባራቸው በማንኛውም ሰው ዘንድ ምን ጊዜም ሲታሰቡና ሲታወሱ የሚኖሩ ሴት ናቸው:: ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ብናዝንም በሕይወት እያሉ የእግዚአብሔር ፍቅር ያደረባቸው ስለነበሩ የዘለዓለም ሕይወት ያለበትን ሰማያዊ ቤታቸውን አዘጋጅተው ያለፉ በመሆናቸው እንፅናናለን:: ቅዱስ ጳዉሎስ "ልሂድ ከክርስቶስም ጋር ልኖር እናፍቃለሁ" እንዳለ ቸሩ አምላካችን ነፍሳቸውን ከፃድቃንና ከሰማእታት ጋር በገነት እንዲያኖርልን ፀሎታችን ነው::
……....……....……....……....……....ምስጋና
……....ወ/ሮ ጥሩነሽ በሕመም ላይ እያሉ ተመላልሳችሁ ለጠየቃችሁ፣ ከውጭ በስልክና በሌሎች የመገናኛ ዘዴዎች በመጠቀም ስታበረታቱን ለነበራችሁ፣ እዚህ በመምጣት በጊዜያችሁ፣ በፀሎታችሁ፣ በምክራችሁና በገንዘባችሁ፣ እውነተኛ ፍቅራችሁን ለለገሳችሁን ሁሉ እግዚአብሔር ይስጥልን እንላለን:: ሕይወታቸው ካለፈም በሁዋላ እዚህ ለመምጣት ባለመቻላችሁ ነገር ግን በመንፈስ አብራችሁ ከእኛ ጋር እዚህ ለነበራችሁ ሁሉ ሳይቀር ጥልቅ ምስጋና ይድረሳችሁ:: ……....……....
…….... ባለቤታቸው አቶ ዮሐንስ ቦሪዮኒ እና ቤተሰብ በሙሉ




ማን ይሆን ዘረኛው?

ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ 04 08 2010


…….... ኢምባራዚስሚ "IMBARAZZISMI" በሚል ርዕስ አንድ የኮንጎ ተወላጅ ምሁር ዘረኝትን አስመልክቶ በህይወት ታሪኩ በሚኖርበት ጣሊያን አገር ውስጥ የገጠመውን ሁሉ በጣሊያንኛ ቋንቋ በመፅሃፍ መልክ አቅርቦታልና አንብባችሁ እንድትደሰቱ በማለት አንዷን ጥቅስ ከዚህ በታች አቀርብላችኋለሁ::
……....Un giorno, in classe, durante un incontro sull'interculturalità, chiesi ai ragazzi di darmi una definizione del termine "razzismo". Subito, il più sveglio esclamò: "Il razzista è il bianco che non ama il nero!" "Bene" dissi. "E il nero che non ama il bianco?" Mi guardarono tutti stupiti ed increduli con l'espressione tipo:"Come può un nero permettersi di non amare un bianco?".
…….... Solo per questo racconto (quanto vi fa pensare e a cosa?), vale la pena di leggere il libro di Kossi Komla-Ebri, cittadino italo-togolese, medico, mediatore interculturale nel mondo della scuola e della sanità, autore di racconti, articoli e saggi. Parole di un italiano riguardo il libro di Kossi Kombla-Ebri:
……....Il testo è costituito da racconti di scene di vita quotidiana, che cercano con un certo spirito ironico ma serio, di illustrarci situazioni di imbarazzismo, cioè di gaffe imbarazzanti o situazioni imbarazzanti legate alla questione della razza e in particolare, in questo caso, alla questione bianco nera (che, come potrete immaginare, niente ha a che vedere con i colori della celeberrima squadra di pallone…).
…….... E' per una volta l'immagine che "l'altro" ha di noi, i suoi sorrisi agrodolci di fronte alla nostra ignoranza, ai pregiudizi e ai tabù, che a volte offendono o feriscono. E' interessante guardarsi allo specchio attraverso gli occhi di Kossi: probabilmente ciascuno di noi, leggendo, si riconosce nella frase stupida di un passante, nel commento ignorante del viaggiatore di treno, nell'illazione superficiale dell'impiegata di tribunale. Ci vuole un'oretta per leggere "Imbarazzismi". Molto più tempo per pensare alla questione che sottende e che riguarda noi tutti, in prima persona. La nostra apertura verso l'altro, il desiderio reale di conoscenza, la consapevolezza di come guardano i nostri occhi e di cosa pronuncia la nostra lingua.
…….... Il libro ha una prefazione di tutto riguardo, a cura di Laura Balbo, che è stata Ministro per le Pari Opportunità e che attualmente insegna sociologia all'Università di Ferrara ed è presidente dell'Associazione Italia-Razzismo.





di Shukri Said, portavoce dell’associazione Migrare 11 06 2010

………Con la ricca Libia, accordi da 5 miliardi di dollari. Nulla invece per Eritrea, Somalia, Etiopia. A questi migranti si nega addirittura il diritto di asilo secondo il Trattato di Ginevra.
………L’orrendo frutto dell’accordo sui respingimenti tra Italia e Libia, alla fine, ha mostrato il suo grado di maturazione spargendo il suo succo amaro sul capo di quasi tutti gli italiani perché l’arco di coloro che a quell’accordo hanno prestato il consenso è stato molto più ampio di quanto ci si sarebbe aspettato.
………Il messaggio in bottiglia costituito da un sms ha permesso al mondo di conoscere la fine che fanno gli abitanti dei Paesi subsahariani orientali respinti dall’Italia senza alcuna selezione tra gli aventi diritto all’asilo e imprigionati nei lager libici in mezzo al deserto tra malattie e torture, con poco cibo, poca acqua, niente igiene e un caldo pazzesco.
………Quanto si è appreso da quell’sms non è affatto una sorpresa, ma la conferma dell’esito annunciato all’indomani della ratifica di quell’accordo tra Italia e Libia e massimamente temuto dalla sua attuazione, quando il 15 maggio 2009 l’Italia donò le prime due motovedette alla Libia proprio per il pattugliamento della frontiera mediterranea. La vergogna di quell’accordo stigmatizzato da tanti della società civile italiana, dall’Ue e dall’Onu, ora ricade su tutti noi e ci impone una riflessione.
………Le vittime dei respingimenti sono soprattutto eritrei, somali ed etiopi. Popoli che, con quello libico, sono appartenuti alle colonie italiane di cui il Fascismo fu tanto orgoglioso da proclamarsi Impero proprio in virtù di esse. L’Italia ha espressamente riconosciuto di aver provocato danni con l’occupazione dei territori africani. Lo attesta il trattato con la Libia alla quale si attribuiscono ben 5 miliardi di dollari di indennizzi. Nulla, però, è stato sin qui previsto per gli altri Paesi occupati nell’epoca coloniale, tanto meno per quelli dell’Africa Italiana Orientale istituita nel 1938 accorpando Eritrea, Somalia ed Etiopia e da cui provengono in gran parte quei profughi respinti in mare dalla Libia cui il Governo Berlusconi ha appaltato la blindatura della frontiera a sud. Anche la conciliazione con il passato coloniale, dunque, si conferma una scelta ad personam, prevedendo il risarcimento in favore della sola Libia, ricca di petrolio e gas, ed a scapito dei Paesi più deboli. Metodo coerente con gli altri dell’attuale Governo: debole con i forti e forte con i deboli. ………L’Italia deve immediatamente modificare le sue scelte e farsi carico dei disperati delle sue ex colonie. Inoltre, più di ogni altro Paese, deve farsi carico di intervenire nelle ex colonie per favorire la loro riorganizzazione ed il miglioramento delle condizioni di vita dei loro abitanti. Questo sarebbe certamente il modo migliore per attenuare la pressione dell’immigrazione che proprio da quei Paesi mira ad arrivare al nostro quale più familiare tra tutti gli altri, sia per lingua che per tradizioni. È assolutamente inaccettabile, invece, non solo rimanere inerti rispetto alla gravità delle condizioni in cui versano i Paesi dell’ex A.I.O. del 1938, mentre si china la testa dinanzi al Colonnello Gheddafi, ma addirittura rigettare in mare i profughi di quei Paesi evitando accuratamente di accertarne il diritto all’asilo secondo i principi del Trattato di Ginevra. ………Tutti gli altri Stati che hanno avuto un passato da colonizzatori si sono fatti carico dei problemi dei territori occupati dopo il riconoscimento dell’indipendenza. L’Inghilterra li ha mantenuti tuttora associati nel Commonwealth, cioè nel benessere comune, in cui si è stabilito un libero o preferenziale diritto di migrazione da un Paese ad un altro. ………La Francia ammise sul proprio territorio, e con la cittadinanza francese, circa un milione e mezzo di pieds noirs che lasciavano i Paesi del Maghreb che nel 1962 conquistarono l’indipendenza e mantenne per decenni facilitazioni alla libera circolazione con le ex colonie. Partecipando al colonialismo al pari di tutte le grandi nazioni dell’epoca, l’Italia volle mostrare al mondo di valere quanto le altre grandi potenze, ma quando si è trattato di assumersi le responsabilità che il colonialismo comportava, l’Italia non solo non ha riconosciuto nessuna facility ai cittadini delle ex colonie al momento di adottare i flussi di lavoratori extracomunitari, ma addirittura ha elevato alle sue frontiere il muro dei respingimenti indiscriminati. migrare@tiscali.it



በጣሊያን የኢትዮጵያውያን ቁጥር 35,000?


09 10 2009

……....ከተለያዩ ሀገሮች ፈልሰው በእያንዳንዱ የአውሮፓ ሀገር ውስጥ የሚኖሩትን የስደተኞች የቁጥር ብዛታቸውንና ዜግነታቸውን በሰንጠርዥ ላይ እንዲሰፍር ያደረገው የአውሮፓው ስለኢሚግሬሽን የጥናት/ፍለጋ ክፍል ነው። በዚህም የአሃዝ ሰንጠረዥ (ስታትስቲክስ) ላይ "በመላው የኢጣሊያ ግዛት ውስጥ ትውልዳቸውና ዜግነታቸው የኢትዮጵያ የሆኑትን በቁጥር እስከ 35ሺ ናቸው" ብሎ በኡኒዩስት የሀምሌ/ነሀሴ የመጽሔት ሕትመት ላይ ሰፍሯል።
……....በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ስለአሉት የውጪ ዜጋዎች፣ ኮሙኒቲዎች፣ ኢንተግሬሽን፣ ዜግነት፣ ብዛትና የመሳሰሉትን ሁኔታ የሚከታተለው ይኸው የኢሚግሬሽን ጥናት ዜግነታቸውና ትውልዳቸው ኢትዮጵያ የሆኑትን ከሌሎች የውጪ ሀገር ዜጋዎች ብዛት አነጻጽሮ በአሰፈረው የቅደም ተከተል ደረጃ ላይ ኢትዮጲያን በ18ኛው መስመር ላይ መድቧታል።
……....አከራካሪ በሆነው በዚህ የአሃዝ ሰንጠረዥ መሰረት 5ሺው የሚኖሩት በሮማና አካባቢዋ ሲሆን ሚላኖና አካባቢው 3 ሺ ኢትዮጵያውያን እንደአሉ በዝርዝር ያቀርባል። በደቡብ ጣሊያን በሚገኙት ሀገሮች ውስጥ ደግሞ በጅምላ ከ5ሺ በላይ ይሆናሉ ብሏል። "ከሮማና ከሚላኖ በስተቀር በታወቁ ትላልቅ ከተሞቿ ውስጥ (ቶሪኖ፣ ናፖሊና ፍሬንዜ) በርካታ ኢትዮጵያውያን እንደሚኖሩባቸውና 10ሺ የሚሆኑትን ይከፋፈሉታል" ማለቱ ያጠያይቃል። የቀረውን 10ሺ ለማን ለማን ከተማ እንደሰጠ ግን አያስታወቅም።
……....ከጥናቱ ማስረጃ (ሰንጠረዡ)ጋር አያይዞ እንደገለጸው ኢትዮጵያውያን በብዛት ተሰደው የሚገኙበት ሀገር በአሜሪካ ውስጥ እንደሆነና ቁጥራቸውንም ወደ 500ሺ ይጠጋሉ ብሏል። በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ እስራኤል 105ሺ፣ በሶስተኛ ደረጃ ሳውዲአረቢያ 90 ሺ፣ ካናዳ 40 ሺ፣ ሊባኖስን ደግሞ ከጣሊያን እኩል በማድረግ በአራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ ብሎ አስፍሯል።
……...."በጣሊያን የኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ቁጥር በተመለከተ ሌሎች መዝገቦችና ጽሁፎች እንዲሁም በስታትስቲክስ ላይ የወጡ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች ለማግኘት ብዙ ያስቸግራል። በእርግጥ ከቀድሞዎቹ መረጃዎች መነሻ በማድረግ በጣሊያን በአለፉት 10 ዓመታት ውስጥ በቁጥር ከእጥፍ በላይ የጨመሩበት ጊዜያት ናቸው። ቢሆንም ይህ የአውሮፓ ኢሚግሬሽን የጥናት ክፍል በአቀረበው መረጃ የኢትዮጲያውያንን ቁጥር ብዛት ከሌሎቹ የአውሮፓ ሀገራት አወዳድሮ ጣሊያንን ቀዳሚ ማድረጋቸው ያጠራጥረኛል። በዜግነታቸው ኢትዮጲያዊ የሆኑትን ብቻ ሳይሆን በትውልዳቸውም ኢትዮጲያ ሆኖ ነገርግን በዜግነታቸው ጣሊያናዊ የሆኑትን ደምሮ የቆጠረ ከሆነ ምናልባት ትክክል ሊሆንም ይችላል። ያም ቢሆን እንኳን እንግሊዝ ውስጥ ብቻ ከ 50,000 በላይ ኢትዮጲያውያን/ት እንደሚኖሩባትና በቁጥርም ጣሊያንን እንደምትበልጥ ብዙዎች ይገምታሉ።...

(ትርጉም +አስተያየት) አብራሃም ዘውዴ (ቦሎኛ)



መመረሽ፣ መፈረሽ፣ መደንበሽ


በዳንኤል ክብረት—ሚላኖ፣ ጣልያን 04 06 2010

……....«በረሃንና ባሕርን አቋርጦ ጣሊያን የመጣ ሰው መጨረሻው ምንድን ነው?» «ወይ ትመርሻለህ፣ ወይ ትፈርሻለህ፣ ወይ ትደነብሻለህ» «ምንድን ነው መመረሽ? ምንድን ነው መደንበሽ? ምንድን ነው መፈረሽ?» «ጣልያን ለመኖር የሚመጣ የለም፣ ስለዚህ ትንሽ ገንዘብ ነገር ቆጣጥረህ ወደ እንግሊዝ ትሻገራለህ፤ ይኼ መመረሽ ይባላል፡፡ ያለበለዚያ ደግሞ እዚሁ የመኖርያ ፈቃድ አወጥተህ የተሻለ ሥራ ካገኘህ ትኖራለህ፤ ይኼ ደግሞ መፈረሽ ይባላል፡፡ ሁለቱም ካልሆነልህ ደግሞ ትጀዝብና ደንብሸህ ትኖራለህ፡፡».........
……....ብዙዎቹ በረሃንና ባሕርን አቋርጠው ጣልያን የገቡት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ሲናገሩ «የሱዳን ሕዝብ ጥሩ ነው፣ ለስደተኞች ይራራል» ይላሉ፡፡ መጀመርያ ወደ ሱዳን ኤምባሲ ሄዳችሁ የመግቢያ ቪዛ ታወጣላችሁ፡፡ ከዚያ በጎንደር በመተማ በኩል ወደ ሱዳን ትገሠግሣላችሁ፡፡ እዚያ ታወቁ ሁለት አሸጋጋሪዎች አሉ፡፡ በአካል አታገኟቸውም፡፡ ስልካቸውን ከሀገር ሳትወጡ ይዛችሁ መሄድ አለ አበለዚያም ጣልያን የገባ ሰው ሊነግራችሁ ይገባል፡፡ አንዳች ሰዋራ ሥፍራ ተደብቃችሁ በስልክ ታገኟቸውና የጉዞ ዋጋ እና ቀን ትነጋገራላችሁ፡፡ እነርሱም ገንዘቡን ይዛችሁ የምትመጡበትን ቦታ እና ቀን ይነግሯችኋል፡፡ በተባላችሁት ሌሊት እቦታው ስትደርሱ እንደ እናንተ በቀጠሮ የመጡ ሌሎች ስደተኞችን ጨምረው በጭነት መኪና ወደ ሊቢያ ድንበር ትወሰዳላችሁ፡፡»
……....ጉዞው ሌሊት ሌሊት፣ ያውም አብዛኛው በእግር፣ ጥቂቱ ደግሞ በመኪና ስለሆነ ከሃያ ቀን እስከ አንድ ወር ይፈጃል፡፡ ሊቢያ ድንበር ስትደርሱ የሱዳን አሸጋጋሪዎች ለሊቢያ አሸጋጋሪዎች ያስረክቧችኋል፡፡ ዋጋ ተነጋግራችሁ አሁንም ጉዞ ትጀምራላችሁ፡፡ ግማሹን በእግር ግማሹን በፒካፕ መኪና፡፡ ደረቅ ዳቦ እና ውኃ ይሰጣችኋል፡፡ መንገድ ላይ የሚሞቱ ልጆች ይኖራሉ፡፡ አሸዋውን ማስ ማስ አድርጎ በመቅበር ጉዞ መቀጠል ነው፡፡ «በእግር ወይንም በመኪና ስትጓዝ በእንጨት የመስቀል ምልክት ተሠራበት ነገር ካየህ እዚያ ቦታ አንድ አበሻ ስደተኛ ተቀብሯል ማለት ነው፡፡» ብሎኛል ጣልያን ያገኘሁት ልጅ፡፡ «ሰው ከታመመ እንደ በሽታው ነው፡፡ መጠነኛ ከሆነ በድጋፍ ይሄዳል፡፡ ከባድ ከሆነ ግን ቁርጥ ወገን ያስፈልገዋል፡፡ ከቡድኑ ከተቆረጥክ ችግር ስለሚያጋጠምህ አንዳንዱ ትቶህ ይሄዳል፡፡ ብዙ ጊዜ ግን የቂርቆስ ልጆች ይተዛዘናሉ፡፡ እንዲያውም
….......…...." ከቂርቆስ ልጅ ጋራ አብረው ቢሰደዱ
…….............ቢያገኝም ያበላል ቢያጣም ያዝናል ሆዱ " ተብሎ ተዘፍኖላቸዋል፡፡» አለኝ ሮም ያገኘሁት የአዲስ አበባው የቂርቆስ ልጅ፡፡ አዲስ አበባ ስለ ቂርቆስ ሠፈር ልጆች አያሌ አስገራሚ እና አስቂኝ ነገሮች እሰማ ነበር፡፡
……....እዚህ ጣልያን ደግሞ አገር ጉድ የሚያሰኝ ገድላቸውን መስማት ጀምሬያለሁ፡፡ ሊቢያ ስትገቡ የተቀበሏችሁ አሸጋጋሪዎች ከትሪፖሊ አጠገብ የገጠር መንደር ውስጥ በተሠራ አዳራሽ አስገብተዋችሁ ይጠፋሉ፡፡ ከዚያ ሌሎች አሸጋጋሪዎች ደግሞ ይመጡና «ትሪፖሊ ሩቅ ስለሆነ እንድንወስዳችሁ መቶ መቶ ዶላር ክፈሉ» ይሏችኋል፡፡ ታድያ የቂርቆስ ልጆች ምን አደረጉ መሰላችሁ፡፡ የተወሰኑት ልጆች ሌሊት ተደብቀው ይወጡና እግራቸው ወዳመራቸው ሲጓዙ ለካስ ትሪፖሊ ቅርብ ነው፡፡ ተመልሰው ይመጡና ሌሎችን ልጆች ነጻ ያወጧቸዋል፡፡ ከእነርሱ በኋላ ለሚመጡት ስደተኞች ደግሞ ግድግዳው ላይ በአማርኛ እንዲህ ብለው ይጽፋሉ «እንዳት ሸወዱ፣ ትሪፖሊ ቅርብ ነው፡፡ ብር ስጡን ቢሏችሁ አትስጡ፡፡ በዚህ እና በዚያ አድርጋችሁ ጥፉ» ይሄ ማስታወቂያ አያሌ ስደተኞችን ታድጓቸዋል፡፡ አይ የቂርቆስ ልጆች፡፡ ነፍስ ናቸውኮ፡፡ ትሪፖሊ ገብታችሁ የመርከብ ወረፋ መጠበቅ ነው፡፡ ክፉ ፖሊሶች ካገኟችሁ በመኪና ጭነው እንደ ገና ወደ ሱዳን ድነበር ወስደው ያሥሯችኋል፡፡ እዚያ እሥር ቤቱ በጣም አሰቃቂ ነው፡፡ እዚያም ቢሆን የቂርቆስ ልጆች ካሉ መከራው ይቀልላል፡፡ ከእሥር ቤቱ ለመውጣት የገንዘብ ጉቦ ያስፈልጋል፡፡ ያንን ደግሞ ለማግኘት ወይ አስቸጋሪ ሥራ መሥራት ያለበለዚያም ደውሎ ከዘመድ ማስመጣት ያስፈልጋል፡፡ እዚያ እሥር ቤት ብዙ ልጆችን ያስፈታ አንድ የቂርቆስ ልጅ ነበር፡፡ ሥራ ይወዳል፡፡ ሲጋራ፣ ብስኩት እና ሳሙና እየሸጠ ይኖር ነበር፡፡ በዚያ እሥር ቤት ብዙ ጊዜ የቆየው ሌሎችን ሲያስ ፈታ ገንዘቡ እያለቀበት ነው ይባላል፡፡ ሌሎች ደግሞ በሌላ ነገር ይተርቡታል፡፡ ከእሥር ቤቱ ሊወጣ በር ላይ ሲደርስ «አንድ ሲጋራ አለህ» የሚል ገዥ ሲመጣ ለርሱ ሊሸጥ እየተመለሰ ነው፡፡ እንዲያውም አንድ ጊዜ በአጥር ዘለሎ ሊያመጥ ሁሉም ነገር ተስተካክሎለት ነበር፡፡ ሊዘልል አንድ እግሩን እንዳሣ «አንድ ሲጋራ አለህ» የሚለውን ሲሰማ ተመልሶ መጣ ይባላል፡፡ በቤንጋዚ ወደብ አሻጋሪዎች እና ተሻጋሪዎች አይገናኙም፡፡ ሃያ እና ሰላሣ ሰው እስኪሞላ የሚመዘግቡ ሰዎች አሉ፡፡ የቡድኑ አባላት ሲሟሉ ገንዘብ ይከፍሉና ወደሚሻገሩበት ወደብ ይወሰዳሉ፡፡
……....የመሻገሪያዋ ጀልባ ብዙ ጊዜ ከቆርቆሮ እና ከእንጨት የምትሠራ ናት፡፡ ለአንዱ ስደተኛ አሻጋሪዎቹ የመርከቧን አነዳድ ያሳዩታል፡፡ ትምህርቱ ቢበዛ ከአንድ ቀን በላይ አይሰጥም፡፡ ለዚያ መከረኛ «ካፒቴን» የጀልባዋን ኮምፓስ አሥረው ካርታውን ያስረክቡታል፡፡ ምግብ እና መጠጥ ይጫናል፡፡ እንደ ጀልባዋ ስፋት ከሃያ እስከ ሠላሳ ስደተኛ ይሳፈራል፡፡ በሌሊት የጣልያንን መብራት በሩቁ እያዩ ጉዞ ይጀመራል፡፡ አሻጋሪዎቹ ጀልባዋ ስትነሣ ይመለሳሉ፡፡ ከዚህ በኋላ እዳው የስደተኞቹ ነው፡፡ ጉዞው እስከ አስራ ሰባት ሰዓት ይፈጃል፡፡ የአንዱ እግር ከሌላው ጀርባ ጋር ተሰናስሎ ተኮራምቶ መጓዝ ብቻ ነው፡፡ ሙቀቱ እና ተስፋ መቁረጡ አንዳንዶችን ራሳቸውን ወደ ባሕሩ እንዲጥሉ ያደርጋቸዋል፡፡ በተለይም መርከቡ መንገድ ከሳተ፡፡
……....የሚያስጎበኘኝን የቂርቆስ ልጅ «ለምንድን ነው ጣልያን ውስጥ የቂርቆስ ሠፈር ልጆች የሚበዙት? እንዲያውም ሮም ውስጥ የቂርቆስ ልጆች ብቻ ያሉበት አንድ ሕንፃ አሳይተውኛል፤» አልኩና ጠየቅኩት፡፡ «ምናልባት የሱዳን ኤምባሲ ሠፈራችን ውስጥ ስለሆነ ይሆናል በሱዳን በኩል እያቋረጥን የመጣነው» አለና ቀለደብኝ፡፡ «ቆይ ግን ለመንገዱ ብዙ ዶላር ያስፈልጋል ሲባል ነበር የምሰማው፤ እንዴት ነው ጉዳዩ» ልኩት፡፡ «ቂርቆስ የድኻ ሠፈር ነው ብለው ስማችንን ያጠፉትኮ የቦሌ ልጆች ናቸው፤ እነርሱ አውሮፕላን ሲያዩ ስለሚውሉ የገዙ እየመሰላቸው ነው፤ እንዲያውምኮ መንግሥት ሀብታም ገበሬዎችን ብቻ ሳይሆን እኛንም መሸለም ነበረበት፤ የመረጃ እጥረት ነው» አለኝ፡፡ «እንዴት?» አልኩት፡፡ «እስኪ ተመልከት እኛ የቂርቆስ ልጆች የመንግሥትን እጅ ሳንጠብቅ፤ አነስተኛ ፣ጥቃቅን ሳንል፤ ራሳችንን በራሳችን ረድተን እዚህ መድረሳችን አያሸልመንም» አለና ሳቀ፡፡ «ሀብታም ገበሬዎች ራሳቸውን ቻሉ እንጂ የሕዝብ ቁጥር አልቀነሱም፤ እኛ ግን ራሳችንንም ቻልን፣ ከሀገር በመውጣታችን ደግሞ የሕዝብ ቁጥር ቀነስን፡፡ ከዚህ በላይ ምን የሚያሸልም ነገር አለ፡፡ አየህ እኛ እንደ ቦሌ ልጆች ጆግራፊን በቲቪ ሳይሆን በተግባር ነው የምንማረው» «ደግሞምኮ የአባቶቻችንን ደም የመለስን እኛ ነን» አለኝ እየሳቀ፡፡ «እንዴት?» «ጣልያን ባሕር አቋርጦ ሀገራችንን ወረረ፡፡ እኛ ደግሞ የአባቶቻችንን ደም ለመበቀል ባሕር አቋርጠን ሀገሩን ወረርነዋ፤ አንተ ቂርቆስኮ የጀግና ሠፈር ነው» አለና ሳቀ፡፡
……....«እውነት ግን ለምንድን ነው የቂርቆስ ልጆች እዚህ የበዛችሁት?» «ምን መሰለህ ይህንን በረሃ ለማቋረጥ ከሁለት እስከ ሦስት ወር ይፈጃል፡፡ የገንዘብ፣ የምግብ፣ የውኃ ችግር አለ፡፡ ካልተዛዘንክ በቀር ይህንን በረሃ ልታልፈው አትችልም፡፡ እኛ ደግሞ ከልጅነታችን ተዛዝነን መኖር ለምደናል፡፡ ስለዚህ እየተደጋገፈክ መጓዝ ነው፡፡ ያው እንግዲህ ባሕር ኃይልም አየር ኃይልም እየመጣ ይቀጥላል» «የቀድሞ ወታደሮችም ይመጣሉ ማለት ነው» «አይ እነርሱ አይደሉም፡፡ በአውሮፕላን ጣልያን የገባው ስደተኛ አየር ኃይል ይባላል፡፡ በባሕር የገባው ደግሞ ባሕር ኃይል ይባላል፡፡ ታድያ አየር ኃይሉ ባሕር ኃይሉን ይንቀዋል፡፡» «ለምን?» «ያው መከፋፈል ለምዶብን ነዋ፤ አታይም መንገድ ላይ እንኳን ጉስቁል ያለ አበሻ ካዩ ሰላም አይሉንም፡፡ ጣልያኖች እንደሆኑ አየር ኃይልም ሆንክ ባሕር ኃይል ሚኒስትር አያደርጉህም፤ ሁሉም ያው ሲኞራ ቤት ነው የሚሠራው፡፡ «ሲኞራ ቤት ደግሞ ምንድን ነው?» «ሰው ቤት ተቀጥሮ መሥራት ማለት ነው፡፡ እዚህ ብዙው አበሻ እንደዚያ ነው የሚሠራው፡፡ ያውም ለሴቶች እንጂ ለወንዶች ሥራ አይገኝም፡፡ ድድ ስታሰጣ መዋል ነው፡፡» «ግን ምን ላይ እየኖርክ ድድ ታሰጣለህ» አልኩት፡፡ «እዚህ አበሻ ከድንኳን ሰባሪነት ወደ ሕንፃ ሰባሪነት ተሸጋግሯል» «እንዴት እንዴት ሆኖ» «ያንን ሁሉ በረሃ አቋርጠህ፤ ባሕር ሰንጥቀህ ጣልያን ስትገባ ምንም ነገር አታገኝም፡፡ ከምግብ በቀር ቤት እንኳን የሚሰጥህ የለም፡፡ ለተወሰነ ጊዜ መጠለያ ውስጥ ያስገቡህና በኋላ ሠርተህ ብላ ብለው ያሰናብቱሃል፡፡ ያን ጊዜ ችግር ውስጥ ትወድቃለህ፡፡ አበሻ ታድያ ይሰባሰብና በልዩ ልዩ ምክንያት የተዘጋ ሕንፃ ያስሳል፡፡ የተወሰነ ጊዜ ሁኔታውን ታይና ሃያ ሠላሳ ሆነህ በሩን ሰብረህ ትገባለህ፡፡ ከዚያ ክፍሎቹን መከፋፈል ነው፡፡» «ባለቤቶቹስ» «ባለቤቶቹ ኡኡ ይላሉ፡፡ ፖሊስ ይመጣል፤ ግርግር ይፈጠራል፡፡ የሰው ልጅ ሜዳ ላይ ወድቆ እንዴት ሕንፃ ተዘግቶ ይኖራል ብለህ ትከራከራለህ፡፡ መቼም የሰው መብት በመጠኑም ቢሆን የሚከበርበት ሀገር ነውና የሰው መፈረሽ መብት ተከራካሪ ድርጅቶችም አብረውህ ይጮኻሉ፡፡ በመጨረሻ ታሸንፍና ትኖርበታለህ፡፡» «መብራት እና ውኃ አይቆርጡባችሁም?» «ብዙ ጊዜ መብራቱን እንጂ ውኃውን መቁረጥ ያስቸግራቸዋል፡፡
……....የሮም ሕንፃዎች የድሮ ሕንፃዎች ናቸው፡፡ የውኃ መሥመሩ በቀላሉ አይገኝም፡፡ መብራቱን ግን ቢቆርጡትም እንቀጥለዋለን፡፡ አንድ ልጅ እንዲያውም በዚያ ምክንያት ሥራ አግኝቷል፡፡» «መብራት በመቀጠል?» «አዎ፤ የቤቱን መብራት ሲቆርጡት በመንገድ ከሚያልፈው መብራት ሌሊት ቀጠለው፡፡ ፖሊሶቹ ሲመጡ ይበራል፡፡ ሄደው ከዋናው ማጥፊያ ቢያለያዩትም ይበራል፡፡ አይተው ስለማያውቁ ግራ ገባቸው፡፡ በኋላ ከመንገዱ መብራት መቀጠሉን ሲያዩ እንዴት ሊቀጠል እንደቻለ ማመን አልቻሉም፡፡ እና ትተውት ሄዱ፡፡ ይሄው ፏ ብሎልሃል፡፡ ልጁም ታድያ ኤሌክትሪክ ሠራተኛ ሆኖ ቀረ»
……....«ሴቶች ሲኞራ ቤት ይሠራሉ አልከኝ፤ ወንዶችስ ምን ይሠራሉ?» «ወንድ ከሆንክ አልፎ አልፎ ነው ሥራ የምታገኘው፡፡ ችግር አለ፡፡ አንዱ አበሻ ሲርበው ሴት ነኝ ብሎ ሲኞራ ቤት ተቀጥሮ ነበር አሉ፡፡» «እውነትክን ነው ወይስ ቀልድ ነው» «እኔ ሲያወሩ ነው የሰማሁት፡፡» «እሺ ከዚያስ» «ልጁ ጢም የለውም፤ መልኩ የሴት ድምጽ ነው፡፡ እንዲያው ልጆች በሌላ ነገር ይጠረጥሩታል» «ምን ብለ» «ነገርዬው የለውም ይሉታል» «እሺ» «እና ጉልበታም ነው፤ ሥራዋን ፉት፣ ጭጭ ነበር አሉ የሚያደርጋት፡፡ አንድ ቀን የሽንት ቤቱን በር ሳይዘጋው ረስቶት፣ ቆሞ ሽንቱን ሲሸና ሲኞራው በሩን ሲከፍት ፌንት ወጣ አሉ፡፡ ነፍሷ ደሞዟን ሳትቀበል ከቤት ወጥታ ጠፋች፡፡ በኋላ ግን እንደዚያ ያደረገው ሥራ ስላጣ መሆኑን ሲኞራው ሲሰማ አድንቆ ካምፓኒው ውስጥ ቀጠረው አሉ» «ተው እባክህ፤ ይሄን የመሰለ ፊልም አይቻለሁ፤ ሲኮምኩ ይሆናል» «ኩምክና አይደለም፤ የሆነ ነው ብለውኛል»
……....«እሺ ይህንን ሁሉ ባሕር አቋርጦ የመጣ ሰው መጨረሻው ምንድን ነው?» «ወይ ትመርሻለህ፣ ወይ ትፈርሻለህ፣ ወይ ትደነብሻለህ» «ምንድን ነው መመረሽ፣ ምንድን ነው መደንበሽ፣ ምንድን ነው መፈረሽ» «ጣልያን ለመኖር የሚመጣ የለም፣ ስለዚህ ትንሽ ገንዘብ ነገር ቆጣጥረህ ወደ እንግሊዝ ትሻገራለህ፤ ይኼ መመረሽ ይባላል፡፡ ያለበለዚያ ደግሞ እዚሁ የመኖርያ ፈቃድ አወጥተህ የተሻለ ሥራ ካገኘህ ትኖራለህ፤ ይኼ ደግሞ መፈረሽ ይባላል፡፡ ሁለቱም ካልሆነልህ ደግሞ ትጀዝብና ደንብሸህ ትኖራለህ፡፡





በጣሊያን የሰው ቤት ሥራ እንደ አረብ ሀገር?

አብራሃም ዘውዴ 05 03 2010

……....በጣሊያን በርካታ የአበሻ ሴቶች የሚሰሩት የቤት ውስጥ ሰራተኛ ሆነው በመቀጠር ነው። ይሄን የስራ መስክ በተለምዶው አንጋገር "ዶሜስቲካ" እንለዋለን። ይህ የዶሜስቲካ ስራ እንደ ኮልፍ እና ባዳንቲ (colf, badanti) አይነት ሥራዎችንም ሊመለከት ይችላል። ነገርግን እነዚህን ልዩ የሚያደርጋቸው በስራተኛውና በአሰሪው መካከል የተለየ ይዘት ያለው ወይም የቀጣሪና የተቀጣሪ ስምምነትን የያዘ የመተዳደሪያ ሕግ ስለሚይዙ ሊሆን ይችላል።
……....ይህንን ርዕስ ለምን በጽሁፍ አቀረብከው ብትሉኝ እናንተም ብትሆኑ ይህንን ችግር ሳትሰሙና ሳታስተውሉ አልቀራችሁም ብዬ ነው:: በጣሊያን ሀገር ለብዙዎች የቤት ውስጥ ሰራተኞች ለሆኑት እህቶቻችን እጣ ፋንታ የሆነውን ችግርና ምሬት ከልኩ ያለፈ ሆኖ ስላገኘሁት ነው። የቤት እመቤቶች (ሲኞራዎች) ወይም የስራ ቀጣሪዎቻቸው በሚያደርሱባቸው የስራ መብዛት ምክንያትና በደል ሲያማርሩ ይስተዋላል። እኔ ከአስተዋልኩዋቸው ውስጥ እህቶቻችን ሲገናኙም ሆነ በስልክ ሲጫወቱ በስራ ቦታቸው ላይ የሚገጥማቸውን ችግሮች ጎልተው የሚሰሙትና በብዙዎቹ አንደበት የሚገለጹት ቅሬታዎች ተደጋጋሚ መሆናቸውን ነው:: በተለይም በአሰሪዎቻቸው (መበደል፣ ያለአግባብ ማሠራት፣ ተጽእኖ፣ የሰዓት ክፍያ መቀነስ፣ ደሞዝ ያለመከፈል፣ ከተወሰነው የሥራ ሰዓት በላይ ማሰራት፣ የእረፍት ፈቃድ መነፈግ፣...ወዘተ... ሁሉ) የሚደጋገሙባቸው ገጠመኞቻቸው ስለሆኑ ችግሩ ዝም ተብሎ የሚታለፍ ስላልመሰለኝ ነው:: ታዲያ መወያየትና እውነቱን ይፋ ማድረግ አስፈላጊ አይመስላችሁም?
……....በእነዚሁ የቤት ውስጥ ሰራተኞች (ዶሜስቲካ) ላይ የሚደርሱባቸው አሉ የሚባሉትንና በወሬ ደረጃ የምንሰማቸውን በደሎች ምን አይነት እንደሆኑ ለማወቅ ብዬ አንዳንድ ሰራተኞችን ለማነጋገር ወሰንኩ። በአሥር ከሚቆጠሩት ወገኖች ጋር ቀጠሮ ይዤ ግማሾቹን በቀጥታ ፊት ለፊት በማነጋገር ሌሎቹን ደግሞ በስልክ በመገናኘት ቃለመጠይቅ አድርጌ በከፊሉ አጠናቅቄአለሁ። በግንኙነቴ ወቅት የተረዳሁት እውነታ በአንዳንድ እህቶቻችን ላይ የደረሱት አሳዛኝ ክስተቶች በጣም የሚያሳዝን መሆኑ ነው:: ታዲያ ከአሥሩ ውስጥ ሶስቱ የሚሆኑት የደርሰባቸውን በደል በንዴት ነው የነገሩኝ። ለምሳሌ አንዲቷ የሰዓት ክፍያዋ ላይ ብዙ ስለተቀነሰባት አጠገቤ ሆና እስከማልቀስ ደርሳለች። ታዲያ የእሷ አሰሪዋ የሆነችው ሲኞራጋ በቀጥታ ሄጄ እንደማነጋግርላት ስነግራት ጊዜ እንባዋን እየጠረገች እንደመሳቅ ብላ... “በል ጭራሽ የባሰ አታምጣብኝ” አለችኝ። ከምርዋ እንደሆነ ለማወቅ ጊዜ አልወሰደብኝም። እኔም ደግሜ "አይዞሽ ምንም አይደርስብሽም፣ ለምን ክፍያውን እንደቆረጡብሽ ምክንያቱን ለማወቅ ብቻ ነው" ብዬ ሳረጋግጥላት ጊዜ እሷም እንደገና ደግማ "ግዴለም አትጠይቅ ደሞ የባሰ እንዳይመጣብኝ እኮ ነው" አለችኝ። በዚህ ችግር ውስጥ ስትወራጭ የኖረችው ከዓመት በላይ ሆናት::
……....ታዲያ ይህ “የባሰ አታምጣ” የሚለው ቃል ዛሬ የሚደርስብንን መከራና ችግር አሜን ብለን እድንቀበል የሚያደርገን ቃል ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ሁልጊዜ የባሰ ሊመጣ እንደሚችል ብቻ የምናስበው ለምን ይሆን? ለምን ለመብታችን ከቆምን፣ የሚሰማንን ከተናገርን፣ ነጻነቴን አላስነካም ካልን የባሰ ሳይሆን የተሻለ ሊመጣ እንደሚችል አናስብም? በሰዓት 10 ኤውሮ እየተከፈለን ስንሰራ ቆይተን ሲኞራዋ ወይም አለቃችን 7 ኤውሮ አድርጌዋለሁ ቢሉን "ለምን?" የምንል ስንት ነን? አዎ! ለዚህም ነው የባሰ እንደሚመጣባት ያመነችውና አሰሪዋን እንዳነጋግርላት ያልፈለገችው። ተከራከረች ተብላ ጭራሽ ልታባርረኝ ትችላለች ብላ ስለምትፈራ ብቻ ነው። ነገርግን የምንኖርበት አገር ህግ አለው ብለን ካሰብን፣ የምንኖረውም በህግ አግባብ፣ የምንሰራውም በህግ ጥላ ሥር ከሆነ ለምን? ብሎ መጠየቅ የሚያስፈራ አይደለም። ሰዓት ሲቆረጥብን ዝም ካልን ወይም ያለ ምንም ምክንያት ክሥራ ተባረሻል ስንባል ዝም የምንል ከሆነ ያለንን መብት ገደብ አላወቅነውም ማለት ነው። ስንበደልም ዝም፣ ስንቸገርም ዝም፣ ብሶታችንን ሁሉ ዋጥ፣ ሳንፈልግ ልምምጥ ውስጥ ሁሉ የምንገባው መብታችንን ባለማወቃችን ነው። ስለዚህ መብታችንን የት ድረስ እንደሆነ በማወቃችንና በማስከበራችን ከህግ ውጭ ምንም ነገር ሊደርስብን እንደማይችል ማወቅ ተገቢ ነው። አንዳንዴም እኮ መብታችንን ለማስከበር ሃይላችንን በማሳየት መቆም አለብን። ስለዚህ የባሰ ቢመጣስ እያልን እየተበደልን የምንኖር ከአለን የተሻለ ሊመጣ እንደሚችል እናስብ።
……....ከዚህ በፊት ሌላዋ የቀን ሥራ በመፈለግ ላይ ያለች ነገርግን የቤት ውስጥ ሰራተኛ የሆነች “እንዴት ነው የሰው ቤት ሥራ?” ለሚለው ጥያቄዬ የመለሰችልኝ ትዝ አለኝ። ይኸውም "የሰው ቤት ሥራ በፈተና የተሞላና የተለያዩ ጫናዎች እንዳሉ አጫውታኝ ነበር። የተሰራበትን ሰዓት ይቆጥራሉ፣ መስራት አለመስራቴን ለማወቅ ምልክት ያደርጋሉ። ታዲያ! ቤትና ንብረታቸውን አይቆጣጠሩ ማለቴ ሳይሆን እንደው ከልክ ያለፉ ነገሮች አእምሮ ይጐዳሉ” ብላኝ ነበር፡፡ አሁን የቀን ሥራ የምትፈልጊው ለምንድነው? ለሚለው ጥያቄዬ ስትመልስልኝ "በቀን ስራ ግዴታዎች ቢኖሩም ይህ ሁሉ መገላመጥና መሠደብ የለም እኮ!" ብላኛለች። ታዲያ እኔ እንደገባኝ ከሆነ ይህ የዶሜስቲካ ስራ ላይ ችግር ሊኖር የቻለበት ምክንያት ከአሰሪው ፍላጎት እና አመለካከት ጋር የራሱ ሂደት ስላለው፤ የሰራተኛውና የአሰሪው ጸባይ አይነተኛ ልዩነቶች ሊኖራቸው ስለሚችል፤ ለዶሜስቲክ ስራ ተብሎ የተቀመረ ልዩ መመሪያዎች ስለሌሉ፤ ወዘተ...
……....ከአንድ ዓመት በፊት ይመስለኛል አንድ ኢትዮጵያዊ በጥርጣሬ ብቻ ከፋብሪካ ሥራው ሲባረር እዚያ ይሰሩ የነበሩ ከአስር በላይ የሆኑ የውጪ ዜጎች በአንድነት ቆመው “ለምን?” ስላሉ ሰራተኛውም ሊመለስ፣ እነሱም ሊከበሩ ችለዋል። ሊያስፈራን የሚችለው ህገወጥ ሥራ የምንሰራ ከሆነ ብቻ ነው። ሊያስፈራን የሚችለው እኛ ራሳችን ህጋዊውን መንገድ ካልተከተልን ብቻ ነው። አንገታችንን የምንደፋው፣ እያየን እንዳላየን፣ የሰማን እንዳልሰማን፣ “ይሁን ግዴለም” እያልን ልናልፍ የምንችለው ምናልባት የሰራነው ጥፋት ካለ እንዳይታወቅብን ወይም ሌላ ምክንያት ኖሮ ሊሆን ይችላል። ከዚያ በተረፈ ግን ህጉን ጠብቀን የተቀጠርን፣ ህጉን ጠብቀን የምንሰራ ከሆነና መብታችን የት ድረስ እንደሆነ ካወቅን “የባሰ አታምጣ” ብሎ መገዛት የለብንም።
……....በአሠሪዎችና በሠራተኞች መሀከል የመተዳደሪያ ሕግ አለ። ይህ ከአለ ደግሞ ከህግ ውጪ ለሚፈጸምብን ጉዳዮች ክስ ልንመሠርት እንችላለን። የሰዓት ክፍያ መቀነሳቸው፣ ደሞዝ ያለመከፈላቸው፣ ከተወሰነው የሥራ ሰዓት በላይ ማሠራታቸው፣ የእረፍት ፈቃድ አለመስጠታቸው፣ ለጉልበት ብዝበዛ ሰለባ ከሆኑ፣ የስራ በደል ከተፈጽመብዎት፣ ወዘተ... የአሰሪና የሰራተኛው የስራ ኮንትራት ላይ ከተዘገቡት ውስጥ ጥቂቶችን ለመጥቀስ ያህል... በተለይም በኮንትራቱ ላይ የደሞዝ፣ የስራ ሰዓትና የስራውን አይነት የሚመለከቱት ጉዳዮችን በግልጽ መቀመጥ እንዳለባቸው ያሳውቃል። ለምሳሌ ሰራተኞች ከተስማሙበት የስራ ኮንትራት ውጪ እንዲሰሩ መገደድ የለባቸውም። ለሰራተኛው ቢያንስ በአንድ ሳምንት ውስጥ የሃያ አራት ሰዓት (ሙሉ ቀን)እረፍት ጊዜ ሊኖረው ይገባል። አሰሪው በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ ከ8 ሰዓት በላይ እንዲሁም በሳምንት ከተወሰኑ ሰዓቶች በላይ ማሰራት እንደማይችል ተጥቅሷል። የሚያሰሩበት ቦታና አካባቢው ለሰራተኛው ጤና ጠንቅ መሆን እንደሌለበት ይጠቅሳል። አሰሪዎችም ቢሆኑ በማስፈራራት እንደፈለጋቸው ክብረነክ እና አድካሚ የሆነ ስራን ማሰራት እንደማይችሉ ተጠቅሷል። ይቀጥላል.....
……....መብትን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ ምክሮችና እርዳታዎች ሊሰጥዎ የሚችሉ የድጋፍ ማህበሮች እንዳሉም ሊያውቁ ይገባል። በተለይም በስራ ቦታ ላይ በጾታ፣ በዘር፣ በባህል፣ በሃይማኖት ወይም በእድሜ መሰረት ምንም አይነት ማዳላቶች እንዳይከሰቱ የሚከላከሉ ህጎች አሉ። በደሎችን ሪፖርት ማድረግ ሕጋዊ በመሆኑ ወደ የዜጎች የምክር ቢሮና የህግ ማእከል ወይም የሰራተኞች ማህበር (sindacale) በመሄድ ምክር ሊያገኙ ይችላሉ። አብዛኞቹ እነዚህ ተቋማት ወይም ማህበሮች የሚሰጡት አገልግሎቶች በነጻ ነው። ወደ እነዚህ አካሎች በመሄድ የተለያዩ መብቶችን ቢያስጠብቅም ይህንን የሚጠቀሙ ብዙ አይደሉም፡፡ ምክንያቱም ብዙዎቹ ለመብታቸዉ ቆመው የሚከራከሩላቸውን ተቋማት መኖራቸውንም እንኳን በደንብ እንደማያውቁ ይናገራሉ። የራሳቸውን መብት ባለማወቅ ዝም ብለው እንደሚበዘበዙ ጉዳዩን በቅርብ በሚከታተሉ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች በሚያወጧቸው አንዳንድ ዘገባዎች ላይ ተመልክቷል። አብዛኞቹ የኢንተግሬሽን ችግርና የዳበረ ዕውቀት የሌላቸው ናቸው:: ከትውልድ ቋንቋቸው ውጭ የማይናገሩ ናቸው፡፡ ይህ በራሱ ትልቅ ችግር ነው፡፡ የጣሊያንኛ ቋንቋን ማዳመጥ፣ መናገር፣ ማንበብና የመጻፍ ዕውቅና እንዲኖራቸውና መብትና ግዴታን በቀላሉ እንዲረዱበት ያደርጋቸዋል።.....
……....በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በተለይም በሰለጠነው ዓለም የባርነት አገዛዝ ቀርቷል ተብሎ ነው የሚታመነው ። ይሁንና በአሁኑ ዘመን በአንዳንድ የአውሮፓ ሀገራት (ጣሊያንን ጨምሮ) ሰዎችን ከልክ በላይ በማሰራት አለአግባብ የሚበዘብዙ እና እንደ ባሪያ የሚይዙ እንዳሉ ተደርሶበታል። የቤት ሰራተኞችን መብት የሚከላከለው የአሰሪና የሰራተኛ የመተዳደሪያ ህግ ተዘርዝሮ የተደነገገ ቢሆንም ዛሬም በዚህ የስራ መስክ የተሰማሩ ዜጋዎች አሁንም በደል እየደረሰባቸዉ ነው። ደሞዝ ያለመክፈል፣ የአካል ጉዳትና የመደፈር ዕጣ ሁሉ የሚያጋጥማቸው አይጠፉም። በአስቀጣሪ ኤጀንሲዎቻቸው የተለያዩ ችግሮች ሳቢያ ከስራ በመፈናቀላቸው ሶጆርኖዋቸውን እንኳን ማሳደስ ባለመቻላቸው አስታዋሽ አጥተው አውላላ ሜዳ የቀሩ አበሻዎች አይጠፉም። እነዚህም እንግዴ ምን ያህል የአዕምሮ ጥቃት እየደረሰባቸው መሆኑን ልትገምቱ ትችላላችሁ።

ነገሩ በዚህ ብቻ እያበቃም እኮ!... እስቲ እናንተም ቀጥሉበት... ቸር እንሰንብት



በጣሊያን የስደት መልካምና መጥፎ ጎኑ

አብራሃም ዘውዴ

…….... የሰው ሀገር ኑሮ መልካምና መጥፎ ጎን ስላለው ማስደሰቱም ሆነ ማማረሩ አይቀርም። የስደት ኑሮ ሲባል የሕይወት ኪሳራ አሊያም በተቃራኒው የአዲስ ሕይወት ምዕራፍ መጀመሪያ ወይም መግለጫ ሊሆን ይችላል። ስለዚህ በመጥፎና በመልካም ጉኑ ሊታይ የሚችልበት ሁኔታ ያለው ነው።
……....በዚህ አምድ ስር በጣሊያን ሀገር ውስጥ የስደት ሕይወት ምን እንደሚመስል ቅኝት በማድረግ ግንዛቤን ለማግኘት እንሞክራለን። ከጣሊያን የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማመላከት ለውጪ ዜጋ ፈታኝ የሆኑትን በርካታ ገጠመኞች ለአንባቢያን አቅርቦ የአስተያየትና የመወያያ መድረክ ለመክፈት ነው። በተጨማሪም በቅርብ ጊዜ ወደ ጣሊያን የመጡ ኢትዮጲያውያን ወጣቶች በሀገሪቱ ውስጥ ያሉትን ሁኔታዎች በምን መልኩ እየተላመዱ እንዳሉ በበለጠ ለመረዳት ያስችል ዘንድ በጣሊያን የጥቂቶችን ኢትዮጲያውያን/ት የስደት ሕይወት ምን እንደሚመስል በአጭሩ በማቅረብ ተመክሮዎች ለማድረግ እንጥራለን። ይህም ደግሞ በቅርብ ጊዜ ወደ ጣሊያን ለመጡትና ወደፊትም ለሚገቡት ስደተኞች አዲስ እዉቀት እንዲያፈሩና ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን ስለሚያገኙበት አዎንታዊ አስተዋፅኦ ያለው ነው። በሁለተኛ ደረጃ እዚህ ጣሊያን ሀገር በኑሮአቸው ብዙ ቆይታ ያደረጉት ኢትዮጲያውያን ነባራዊ ልምዳቸውን እንዲያካፍሉ በጣሊያን የስደትን አካሄድና ተለዋዋጭ ፖሊሲዎችን በወቅቱ በማስገንዘብ በዚህ አምድ ላይ አስተውጽኦ እንዲያደርጉ ይጋበዛሉ። ግን ከሁሉም አስቀድሞ ስደተኛ ማለት ምንድን ነው? ማነውስ ስደተኛ? ከአገሩ ወጥቶ የሄደውን በሙሉ ስደተኛ ማለት ይቻላል። ለምሳሌ ለትምሕርት ወይም ለሥራ የወጣውን ስደተኛ ነው ማለት ይቻላል?...
...ይቀጥላል...
……....በጣሊያን ሀገር የሚኖሩት የውጪ ዜጋዎች ከአብዛኛዎቹ የአውሮፓ ሀገር ስደተኞች ኑሮ ጋር ሲወዳደር ኑሮዋችውን የሚገፉት ከብዙ ችግሮች ጋር ነው። በቋንቋና በዜግንት ችግር ምክንያት የስራ እድል ማጣት፤ ከአስተናጋጁ ማህበረሰብ የአኗኗር ዘይቤ ጋር ያለመላመድ ሁኔታ (integrazione)፤ ከአገሪቱ የሥራ ባህል ጋር መላመድ አለመቻል፤ በሚፈልጉት የሥራ አይነት ላይ ቦታ ያለማግኘት፤ የኑሮው ሁኔታዎች መዛባትና አለመመቻቸት፤ የመጠለያ፣ የመኖሪያ ፍቃድ፤ የስራ አጥነት፣ የኢኮኖሚ እጥረት፣ የመፈናቀል፣ የትምህርት፣ የዘረኝነት መድልዎ፤ የቤተሰብና የሀገር ናፍቆት፤ የጤና መታወክና የስነ ልቦና ቀውስ ችግሮች፤ የተራርቆ መኖር፣ እራሱ በሚፈልገውና በሚመኘው የሥራ አይነት አለመሰማራቱ ወይም ልምድና ችሎታ በሌለው የማንኛውም ሥራ ቅጥረኛ በመሆኑ በኑሮው ላይ ምንም አይነት ርካታ አለማግኘት፤ ወዘተ... ተጠቃሾች ናቸው። ...ይቀጥላል...(የተቆረጠው የሚታረም ስለአለበት ነው)

ከ18 እስከ 24 አመት ያላቸውን ወጣቶችን እንዲሁም አዋቂዎችን አነጋግረናል፡፡...

አደንዛዥ እፅ ላይ የወደቀው


……....ጣሊያን ሲመጣ በሃያዎቹ እድሜ ክልል ውስጥ ነበር። የተስፋ ብሩህ ሕይወት ሰንቆ ከአገሩ የወጣው ይህ ሰው ዓላማና ፍላጎቱን ምኞትና ፍቃዱን ለማሳካት ሲጥር ዘጠኝ ዓመቱን አስቆጥሯል። ዓላማውን ከግብ ለማድረስ ቢፈልግና ምኞቱን ለማሳካት ቢጥርም ሁኔታዎች ግን አልፈቀዱለትም። ለመጀመሪያዎቹ አምስት አመት ያህል የመኖሪያና የስራ ፍቃድ ወረቀት ስላልነበረው እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉትን እድሎች ለማግኘት አልቻለም። ለነገሩ እድሉ እያላቸውም ቢሆን በዜግንት፣ በቋንቋ ችግር፣ ሊያገኙ የሚገባቸውን የስራ እድል የሚነፈጉ በርካቶች ናቸው። ይኸው ሰው የስራና የመኖሪያ ፍቃድ ወረቀቱን ያገኘው የዛሬ አራት ዓመት ነው። ይሁን እንጂ ከዚያ በፊት በአሳለፈው የመከራ ሕይወቱ ባጋጠመው የስራ ማጣት፣ የዘር መድሎዎና የማግለል ሁኔታ ችግሮች በደረሰበት የስነ ልቦና ቀውስ ትዕግስትና ጽናቱን አጥቷል። ያለበትን ከፍተኛ ጭንቀትና ሃሳብ ያቃልልኛል በሚል እዚሁ ጣሊያን ከገባ በህዋላ ቀስ በቀስ ከጀመረው የሲጃራ ሱስ ወደ አደንዛዥ እጽ አሳድጎ ዛሬ ባለሱሰኛ ሆኗል። በጥቁር ስራ (በድብቅ ዋስትና የሌለው ስራ) ከሚያገኛት አነስተኛ ገቢውም በከፈተኛ ወጪ የሚገኘውን አደንዛዥ እጽ ህሊናውን አናውዞና ራሱን ደብቆ ይገኛል።... በጸጸትና በንዴት አንድ ቀን ራሱን እንዳያጠፋ ስጋት እንዳለው ለቀረበው ስው ሁሉ በሃዘን ያወራል። ..."ለወረቀት ብዬ የፈጠርዃቸው የውሸት ታሪኮቼ ብዛትና ወሰን የላቸውም። ለመኖር ብዬ እድሜዬንና ስሜን ሁሉ ቀይሬአለሁ። ...
መከራን ተጋፍጦ ኑሮው የተሳካለት
……....በሮማው የስደት ህይወቱ ብዙ ችግሮችን አሳልፏል። አሁን የሚገኘው በሰላሳዎቹ መጨረሻ የዕድሜ ክልል ውስጥ ሲሆን ስደት ለእርሱ ታላቅ የሕይወት ትምህርት ቤትም ነው። በዚህ እጅግ ፈታኝ የስደት ሕይወቱ ተደስቶ አዝኗል፣ አግኝቶ አጥቷል፣ ስቆ አልቅሷል፣ ተጽናንቶ ተማሯል፣ ታግሶም ተስፋ ቆርጦም ያውቃል። ይሁን እንጂ ዓላማውን ለማሳካት ሁሌም ከመትጋት አልተቆጠበም። አገር ቤት እያለም በልጀነቱ ይመኝ የነበረውን ለመሆን የሚያስችለውን የትምህርት እድል አግኝቶም ስራ ሳይንቅ ያገኘውን አይነት ስራ እየሰራ የተሻለ ደረጃ ለመድረስ በትጋት ጸንቷል። ከአልባሌ አሳሳች ድርጊቶች ራሱን በማግለል የጋጠሙትን ፈታኝ የሕይወት ውጣ ውረዶች በትዕግስትና በመንፈሰ ጠንካራነት እየወደቀም እየተነሳ በድል አድራጊነት ተወጥቷቸዋል። የጀመረውን የኤሌክትሪክ ኢንጅነሪንግ ትምህርት አንዳንዴ ጊዜ በማይሰጡ ጠንካራ የሕይወት ገጠመኞች ሲገደድ እያቋረጠ ሲመቸው ደግሞ እየቀጠለ ለማጠናቀቅ በቅቷል። ዛሬ በዚሁ በተመረቀበትና ከልጅነቱ ይመኘው በነበረው ሙያ በሮማው አየር መንገድ ኤለክትሪሻን ኢንጀነሪንግ ሆኖ በከፈተኛ ደሞዝ እየሰራ ይገኛል። ከራሱ አልፎ ለቤተሰቡ ብሎም ለአገሩ እጅግ የሚያኮራ እንዲሁም በስደት ሕይወት ለበዙዎች መልካም አርአያ ለመሆን በቅቷል። ይህ ሰው ጋር ትዳር መስርቶ የአንድ ወንድ ልጅ አባትም ነው።
ለከፍተኛ ትምህርት የማይሞት ተስፋ ያላት
……....አገር ቤት እያለች ምንም ያልጎደለባት፣ ደህና ገቢ ያላቸው ቤተሰቦች ያልዋት፣ ትምህርቷንም እስከዩኒቨርስቲ ለማጠናቀቅ ትንሽ የቀራት ልጅ ናት። እዚህ ጣሊያን አገር ከዘመድ በተላከ የጉብኝት ቪዛ ትመጣና ልመለስ ወይስ ልቅር በሚል ጥያቄ ስታመነታ የጉብኝት ቪዛዋ ያልቃል። በአንድ በኩል የመመለሷን ነገር እንዲሁ ስታወጣ ስታወርድ በሌላ በኩል ደግሞ ይህን እድል ለተሻለ ነገር ልጠቀምበት በሚል ፍላጎት የስራና የመኖሪያ ፍቃድ ለማግኘት አመልክታ መልስ ስትጠብቅ ሶስት ዓመት አለፋት። ስራ ተቀጥሮ ለመስራት ብትፈልግም እንኳን ህጋዊ ወረቀት የሚያስፈልግ በመሆኑ ስላልሆነላት በጥቁር ስራና (በድብቅ ዋስትና የሌለው ስራ) በተባራሪ እዚህና እዚያ እየሰራች ትኖራለች ማለት ነው። እናም ይህ የስደት ሕይወቷ የከፍተኛ ትምህርት የነበራትን ህልም እንዳመከነባት በጸጸት ትናገራለች አትመለስ ነገር አንድ ጥሩ ነገር በእጄ ሳልይዝ እንዴት የሚል ሙግት ውስጥ ትገባለች። ከዛሬ ነገ የጣሊያን ዜግነት አግኝቼ ትምህርቴን ለመከታተል ወይም የተሻለ ሕይወት እንዲኖረኝ በሚል ተስፋ ትኖራለች።
በቤት ሠራተኝነት ተቀጥራ የጾታ ጥቃት የደረሰባት
……....ያገኘናት የአንድ ትልቅ መርካቶ ገበያ አዳራሽ ውስጥ የጽዳት ሥራ እየሠራች ነበር፡፡ ጣሊያን የመጣችው ከ4 ዓመታት በፊት ነው፡፡ ተወልዳ ያደገችው አቃቂ ውስጥ ሲሆን ቤተሰቦቿ በልጆች ብዛት ምክንያት ኑሮ ከእለት እለት እየከበዳቸው ሲሄድ ወደውጪ ሀገር ወጥታ ያገኘችውን ሠርታ ቤተሰቧን ለመርዳት አሰበች፡፡ የተለመደውን የበረሃና የባህር ጉዞ ተጋፍጣ የመጣች ኢትዮጲያዊት ነች። እንደመጣች የመጀመሪያዎቹ ዓመት ውስጥ የተለመደውን የጥቁር ሥራ በቤት ሠራተኝነት ሰርታለች፡፡ "የመጀመሪያው ዓመት በሽማግሌ ጥበቃ በሁለተኛው ዓመት ላይ በተመላላሽ በአንድ ቤተሰብ ውስጥ 3 ህጻናትን በመጠበቅ ከዚያ በህዋላ ደግሞ በተለያዩ የሰው ቤት ውስጥ በመቀጠር በቤት ሠራተኝነት ጀመርኩኝ። ብዙም ጥቂትም ቤተሰብ ያለበት ቤት ውስጥ ተቀጥሬ ሠርቻለሁ፡፡ በዚህ ሁኔታ አራት ዓመት ሆነኝ፡፡ ከዚያ በላይ ግን መቀጠል ስላልቻልኩ ከቤት ስራ ወጥታ የቀን ስራ ተቀጠርኩ" አለችን። "ይህንን የቀን ሥራ (የጐልበት ሥራ) ከመጀመሬ በፊት በሰው ቤት ሠራተኝነት ያሳለፍኳቸው ዓመታት ቀላል አልነበሩም" ስትለን እኛም "እንዴት?" ብለን ላቀረብንላት ጥያቄ ስትመልስልን "ምክንያቱም በየገባሁበት ቤት ከሚሞከርብኝ የፆታ ጥቃት ራሴን ለመከላከል ብዙ ፈተናዎችን አይቻለሁ፡፡ አንዳንድ ቤት ጐረምሳ ልጆች ሌላ ቤት ደግሞ የቤቱ አባወራዎች ያስቸግራሉ፡፡ ልጆቹ እንዲህ ያደርጋሉ ብዬ ስናገር፣ የእኔ ልጅ በጭራሽ ይላሉ፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ባሎች እንዲህ ያደርጋሉ ብሎ ለሚስት መናገር ደግሞ ከባድ ነው፡፡ የተባለውን ነገር ሚስት ላትቀበል ትችላለች፡፡ ትዳራቸውም ሊረበሽ ይችላል" ትላለች፡፡ እንደምትለው "የቤት ሠራተኝነት በቃኝ" ብላ ወደ ቀን ሥራ እንድትሄድ ያደረጋት ይህ ብቻ አይደለም፡፡ በስራዋ ምንም አይነት የእረፍት ቀን እንደማይሰጧትና ትርፍ ጊዜ እንደሌላት አጭውታናለች። ጓደኛ የላትም። ስራዋን በጊዜ አጠናቅቃ ለመጨረስ ደፋ ቀና ስትል አንዳንዴም የጤና ችግር እንኳን ሲኖርባት የእረፍት ጊዜዋን መሰዋት እንዳለባትና መቅረት እንደሌለባት አሠሪዎቿ ያስጠነቅቋት ነበር፡፡ የምመገበውን ምግብ በመለየት እንዲሁም ከጥርጣሬ የተነሳ በአሠሪዎቿ በተለይም (በሚስቶች) የሚደረግባት ያልተገባ ድርጊት ዳግም ወደ ቤት ሠራተኝነት እንዳትመለስ እንዳደረጋት ትናገራለች፡፡ "አብዛኞቹ አሰሪዎች ወደገበያ እንኳን ስንወጣ እንደ ችግር ነው የሚያዩት፡፡ መሥራት ያለብንን ሠርተን ካጠናቀቅን ወደ ውጪ ቢወጣ ችግሩ ምን ላይ ነው? እንዲያውም ሰው በጥሩ ሲለወጥ ማየትን የመሰለ ጥሩ ነገር ያለ አይመስለኝም" በማለት የሰው ቤት ሠራተኝነት በቃኝ በማለት የቀን ሥራ ከጀመረች ሰባት ወር እንደሆናት ገልፃልናለች፡፡ ጥቂት የማይባሉ የቤት ሠራተኞች እንደእሷ ወደ ቀን ሥራ እየገቡ መሆናቸውን የምትናገረው የጉልበት ሥራ ለሴት ልጅ አድካሚ ቢሆንም በነፃነት በመሥራትና በሌሎችም ነገሮች የቀን ሥራ የተሻለ እንደሆነ ታምናለች፡፡ በዚሁ ስራ በወር እስከ 1 ሺ ኤውሮ ይከፈላታል፡፡ በሳምንት አንድ ቀን ታርፋለች፡፡ ለቤት ኪራይ በወር 550 ኤውሮ ትከፍላለች፡፡ "ይህንን ኪራይ በየወሩ መክፈል ቢከብደኝም ያችን ተሯሩጬ ካገኘሁ ባልበላም ቤተሰቦቼን ረድቼ በሠላም ተኝቼ አድራለሁ፡፡ ይህ ደግሞ ከምንም በላይ ለእኔ ከሰው ቤት ሠራተኝነት የተሻለ ነው" ትላለች።
"ከሰው ቤት ሥራ የቀን ሥራ ይሻላል" የምትለው
……....ትእግሥት ትባላለች፡፡ ጣሊያን ስትመጣ ከወንድሟ ጋር ተቀምጣ ለመማር በማሰብ ነበር፡፡ ወንድሟም እንደመጣች ሠው ቤት አስገባት፡፡ ስራ ለመቀጠር ብላ የአስራስድስት እድሜዋን በሁለት ዓመት አሳድጋዋለች:: እንዴት ነው የሰው ቤት ሥራ? ለሚለው ጥያቄ ስትመልስ "የሰው ቤት እኮ በፈተና የተሞላ ነው፡፡ የተለያዩ ጫናዎች አሉ። የተሰራበትን ሰዓት ይቆጥራሉ፣ መስራት አለመስራቴን ለማወቅ ምልክት ያደርጋሉ። ታዲያ! ቤትና ንብረታቸውን አይቆጣጠሩ ማለቴ ሳይሆን ከልክ ያለፉ ነገሮች ግን አእምሮ ይጐዳሉ፡፡ እንደዚህ ዓይነት ነገሮችን እያሳለፍኩ ነው" ብላለች፡፡ በሠራችበት ቤትም ፆታዊ ጥቃቶች ይሞከሩባት እንደነበርም ትገልጻለች፡፡ በትርፍ ሰዓት እንኳን የሀገር ቤት ወገኖቿን ወይም ጓደኞቿን መከታተል አትችልም፡፡ ወደ ቀን ሥራ ከመግባቷ በፊት የነበረችው ሁለት ልጆች ያሉበት ቤት ሲሆን በወር 800 ኤውሮ ይከፈላታል፡፡ አሁን የቀን ሥራ የምትፈልጊው ለምንድነው? በቀን ስራ ግዴታዎች ቢኖሩም ይህ ሁሉ መገላመጥና መሠደብ የለም፡፡ በዚህ እድሜሽ ትምህርት ብትከታተይስ? አልናት፡፡ እሷም ስትመልስን "ሰው ቤት እየሰራሁ እንዴት ይቻላል? ደከመኝ አልቻልኩም" በማለት መልሳልናለች፡፡ ...
"በፖለቲካ ጥገኛነት ምክንያት ኢትዮጵያ ተመልሼ ቤተሰቦቼን ማየት አልችልም"
……....የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን አቋርጦ ነው ወደ ጣሊያን የመጣው፡፡ እዚህም የሀገሪቱ የፍልሰት ፖለቲካ፣ ህግና ሥርዓት አላንቀሳቅስ ብሎት በእጁ ምንም የለውም። ገና እንደገባ እዚሁ ለመቅረት በመወሰኑ መንግሥት እንደሚከታተለው አድርጎ መረጃዎችን በማቅረብ በጣሊያን የፖለቲካ ተገን ማመልከቻ አስገብቶ ውሎ አድሮ ጥያቄው ተቀባይነት አግኝቶ የፖለቲካ ጥገኛ ሆኖ እየኖረ ይገኛል፡፡ ሕይወቱን ለመቀየርና የተሻለ ኑሮ ለመኖር በጣሊያን መቅረትን እንደአማራጭ የወሰደው አሁን ወደ አገሩ መመለስ እንደማይችል ያስረዳል፡፡ በጣሊያን ተገን ሲያገኝ የግድ የነበርውን ፓስፖርት እንዲያስረክብ ተጠይቆ ተተኪ ዶኩሜንት ተሰጥቶታል፡፡ በዚህ ዶኩሜንት በጣሊያን ውስጥ እንደፈለገው መንቀሳቀስ ይችላል፡፡ ነገር ግን የተሰጠው የመቆያ ዶኩሜንት ወደ ኢትዮጵያ መግባት እንዳይችል ያደርገዋል፡፡ ወደኢትዮጵያ ለመመለስ እንኳን ቢፈልግ በዚህ ዶኩሜንት ምክንያት መመለስ አይችልም። ስለዚህ ወደ ኢትዮጵያ የመግቢያ ፍቃድ ማግኘት አይችልም፡፡ "በመጀመሪያዎቹ ጥቂት ዓመታት ይህ ምንም አልመሰለኝም ነበር፡፡ አሁን ግን ነገሮች ከብደውኛል፡፡ እናትና አባቴን፤ ዘመድ ወዳጆቼን ለማየት መምጣት እፈልጋለሁ፡፡ ነገርግን የተሰጠኝ ዶኩሜንት ምክንያት ወደ አገሬ እንዳልገባ የሚከለክል ነው" በማለት ያስረዳል፡፡ አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን ጓደኞቹ በእንደዚህ ዓይነት ችግር ውስጥ ሆነው ከአገራቸው እንደሚርቁ፤ ወደ አገር ቤት ሄደው ቤተስቦቻቸውን ለማየት የመንግሥት መቀየርን በናፍቆት እንደሚጠበቁም ይገልፃል፡፡


...///...

……....ስደት የማኅበራዊ፣ የሰብአዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳይ የሚያስከትለውና ሁሉንም አገሮች የሚመለከት ክስተት ነው። ስደተኛ ሃብት እንጂ ችግር አለመሆኑ መታወቅ አለበት። ......ይቀጥላል... ……....ይሻላል ብለን የመረጥነው ወይም ተገደን የገባንበት "የስደት ዓለም " ምን ያህል ምስቅልቅሉ የወጣ እና የተንበዛበዘ እንደሆነ እንዲሁም የስንቶቻችንን ህይወትና ህሊና እንዳመሳቀለው ሁላችንም እናውቃለን። በቆራጥነትና በደፋርነት የተወጣናቸው ውጣ ውረዶች አልፈን ወደ አስብነው ግብና ዓላማ ደርሰን የምንኮራበት ታሪክም ሊኖረን ይችላል። በተቃራኒውም የምናፍርበትና የምንጸጸትበት ታሪክ ሊኖረንም ይችላል። ለመኖር መብላት፣ ለመብላት መግዛት፣ ለመግዛት መስራት፣ ለመስራት ወረቀት፣ ለወረቀት አንዳንዴም ውሸት አድርገን ዛሬ ያለንበት ቦታ የደረስን ስደተኞችም አለን ለማለት ነው። ይህ ሁሉ እንግዴህ ይኸው የስደት ኑሮ ህሊናችንን ብቻ ሳይሆን ጊዜያችንን እንዴት እንክት አድርጎ እንደበላው ለማስታወስ ነው።...
...ይቀጥላል...
……....የሰው ልጅን ከፍ የሚያደርገው መሰረታዊው እውቀቱ ብቻ ሳይሆን ከህብረተሰቡ ጋር ተዋህዶ አብሮ ለመኖር መቻሉ ነው። በሚያስተናግዱን ህብረተሰቦች ውስጥ ተቀባይነትን ለማግኘት የምንጠቀምንበት ዋነኛው ዘይቤ በጥሩ ስነምግባር አብሮ በመኖር ነው። የተሻለ የስደት ሕይወት ልንመራ የምንችለው ከሚያስተናግደን ማህበረሰብ የአኗኗር ዘይቤ፣ የሥራ ባህል፣ ቋንቋ፣ ... ተላምደን ስንኖር ነው። ስለዚህ ወደ ውጪው ሀገር ስንሄድ በቆይታችን ጊዜ ከአገሩ ሁኔታ ጋር ራሳችንን ለማመሳሰል መሞከር ይገባናል:: እኛ ኢትዮጲያውያን የቤተሰብ፣ የህዝብና ያገር ፍቅር የሚያጠቃንና በዚያ መንፈስ ምክንያት የምንንገላታ አንጠፋምና ያን ተረድተን ብቸኝነትን ጨርሶ ከላያችን ላይ አስወግደን እንደአገሩ መምሰል የግድ ይለናል::በዚህ በኩል የኢትዮጵያ ኮሙኒቲዎች ከአዲስ መጤዎች ጋራ ከፍተኛ ትብብሮች ሊያደርጉ ይገባል:: ህይወታችንን የሚያበላሽ ነገር ውስጥ ላለመግባት የምንችለውን ያህል እንጣር ......ይቀጥላል...

የጥገኛነት ኑሮ በጣሊያን የሶስት አበሾች ምስከርነት

Vita da rifugiato. Le testimonianze 15 05 2009

………ብዙውን ጊዜ በጣሊያን የሚገኙ ስደተኞች የሰበዓዊውም ሆነ የፖለቲካ ጥገኝነት ወይም በጣሊያን ተገን ጠይቀው ከተፈቀደላቸው በኋላ ኑሮአቸው የሚሻሻል ሊመስላቸው ይችላል። ለዚህም ተቃራኒ ምስክር ሆኖ የሚገኘው እነዚሁ ጥገኞች በየትላልቅ ከተሞች ውስጥ በየጊዜው በአደባባይ ላይ እየወጡ የሚያሰሙት አቤቱታዎች ናቸው። በተለያዩ መጠለያ ጣቢያና መስፈሪያዎች የሚገኙት ወገኖችም ከሚያሰሙአቸው አቤቱታዎች መሀከል "ህክምና የለንም፣ ራሽን ተነፍገናል፣ መጠለያ የለንም" የመሳሰሉት ናቸው። በተለይም በዚሁ ሳምንት በሚላኖው የአደባባይ ማኒፌስት ላይ ከመፈክሮቻቸው መሐከል “የጥገኞች መስተንግዶ ከእሥርቤት አይተናነስም” የሚለው አንዱ ነበር። ጋዜጠኛው Giampaolo Musumeci በሚላኖ ከ200 በላይ ሆነው ሰልፍ ከወጡት መሀከል የሶስቱን አበሻዎች ምስክርነት ከዚህ በታች እንዲህ ያቀርበዋል...

...Ecco tre storie di rifgugiati che vivono in Italia che abbiamo raccolto Testo e foto di Giampaolo Musumeci

……… Mikies è un rifugiato di 21 anni, è eritreo e viene da Asmara dove ha lasciato i genitori, una sorella e un fratello. Da sei mesi è a Milano, da un anno in Italia. La sua casa ora è il Parco di Porta Venezia. Mikies, dopo aver lasciato la sua terra, ha vissuto la durezza della prigione libica di Kufrah, nel deserto, dopo essere stato catturato: “I poliziotti libici ci picchiavano, quasi tutti i giorni, uomini e donne, senza motivo”. Ha rischiato la vita durante il viaggio di tre giorni in mare alla volta di Lampedusa. “Sono partito perché volevo solo la libertà, ma ora vorrei una casa e un lavoro. Certo, in Norvegia e nei paesi del Nord Europa, essere rifugiati è un’altra cosa. Ti danno una casa e ti permettono di lavorare” dice. ……… Medhani ha 27 anni ed è di Asmara. È a Milano con la sorella e un nipotino di due anni. È in Italia dal 2004: Ha lasciato l’Eritrea perché contrario alla guerra “Ero un militare in Eritrea ma non volevo andare a combattere quella guerra. Se torno, mi sparano”. Non sa cosa fare: non trova lavoro, non trova casa. Una cosa è certa: di tornare indietro “non se ne parla nemmeno”. ……… Mukahmil ha 22 anni ed è etiope di Addis Abeba. “Sono in Italia da due anni e sette mesi. Sono riuscito a lavorare solo 5 mesi girando tra Verona, Trento, Bolzano, Roma e Milano. Facevo il magazziniere. Ogni giorno faccio chilometri per chiedere a tutte le agenzie interinali e cooperative se c’è un lavoro, ma nulla”. La sua storia è da brividi: “Ho passato due anni in prigione a Kufra senza poter comunicare coi miei familiari. Ero così debole e malconcio che non riuscivo nemmeno a camminare. Poi ho lavorato ancora a Kufrah e Bengasi per poter guadagnare i soldi per arrivare a Lampedusa. Alla fine sono stato tre volte nelle prigioni libiche. E l’ultima volta mi hanno rilasciato perché ho pagato 400 dollari”.

LAVORATORI STRANIERI IN PIAZZA

«VERSO IL MOVIMENTO 1° MARZO?»

Dr. Zeleke Eresso


…….... Giallo è il colore scelto per celebrare questa splendida prima giornata di sciopero nazionale dai lavoratori stranieri, 4,8 milioni quelli presenti in Italia, una tinta svincolata dai partiti politici che nel linguaggio cromatico significa cambiamento.
…….... La maggior parte di queste persone, di seconda generazione, «2G» cosi detto second generation, che ieri hanno «occupato» sessanta piazze italiane per ribadire l’urgenza di un riconoscimento dei loro diritti, molte volte violati e negati. …….... Per l'occasione diverse piazze hanno assunto i colori della protesta, 60 lungo tutto lo Stivale, a partire dalla Capitale dove un corteo animato dall'associazionismo, dai sindacati e dagli immigrati è confluito ieri pomeriggio a Piazza Vittorio Emanuele dove è stato allestito un palco per urlare a gran voce i diritti, troppo spesso soffocati, dei lavoratori stranieri e per dire 'no' al razzismo. La manifestazione, che ha animato un corteo lungo le vie del centro, si è conclusa con un simbolico lancio in aria di palloncini gialli. ……....Gli organizzatori del 'Comitato Primo Marzo' hanno preso a modello quanto fatto in Francia, uno sciopero solo simbolico ma che vuol far comprendere agli italiani quanto importante sia l'apporto degli stranieri nella vita del Paese. E per denunciare una crescente distanza, quella tra italiani e immigrati, che secondo gli organizzatori è stata evidenziata dagli scontri di qualche tempo fa a Rosarno. ……....L'Iniziativa nasce all'indomani dei fatti di Rosarno, le coscienze del movimento anti-razzista italiano si sono svegliate, sottolinea Angela Scalzo, segretario generale di Sos Razzismo Italia. ''Insieme abbiamo creato un movimento che ha dato vita alla 'Primavera anti razzista' all'interno della quale sono affluiti gli associazionismi immigrati e italiano oltre ai sindacati. Noi manifestiamo contro una legislazione discriminatoria com'è quella italiana''. ……...."Andrebbe fatta una riflessione sul tema economia e immigrazione considerato che il 9,5% del prodotto interno lordo è direttamente o indirettamente legato all'immigrazione" ha osservato il direttore della Camera nazionale dell'Artigianato di Roma, ……....Mi auguro infine, che il comitato primo marzo si trasformi, al più presto, in un movimento che è in grado di difendere tutte le persone oggi indifese e invisibili in Italia.

Bologna, 02 marzo 2010


1° Marzo 2010 a Bologna


Cosa succederebbe in Italia se i lavoratori immigrati scioperassero? Ieri, 1 marzo 2010, è stato il giorno del primo sciopero nazionale degli stranieri, con il quale si è voluto dimostrare che i lavoratori immigrati, le loro famiglie e i loro figli sono parte integrante e fondamentale dellla società italiana. CrossingTV ha dato voce ai partecipanti alla manifestazione che ha visto la partecipazione di migliaia di persone. Interviste di Gaia Roncarelli Riprese e montaggio di Silvia Storelli Ringraziamo tutti gli intervistati



በጣሊያን ስደተኛ አበሻ ላይ ቀልዶች

……....ከምንወደውና ከሚናፍቀን ቤተሰብ መራቃችንና መለየታችን፣ የብቸኝነት ኑሮን ስለምንገፋ፣ የሩጫ ኑሮ ስለምንኖር፣ ኑሮው የማይደላ፣ እረፍት የሌለውና ለመንፈስ የማይሞላ በመሆኑ ድብርቱ እንዳለ እናውቀዋለን። በዚህም ምክንያት የሣቅ ችግር አለብን አይደል! ታዲያ ይህንን ድብርት ለማላቀቅ ባገኘነው ዘዴ በመጠቀም አንዳንዴም እንሣቅ እስቲ! ፈገግታ ጥሩ ነው። በስራና በትምህርት የተጨነቀን አዕምሮን አንዳንዴም ለማዝናናት ያህል ከማህደሬ ውስጥ ቆንጥሬ ያወጣኋቸውን ቀልዶች አንብቡና በእኔ ሞት እስቲ ሳቁልኝ:: ቀልዶቹ በሙሉ ጣሊያን ሀገር ያለነውን አበሻ ነው የምመልከተው

PimpingYourSpace.com. All you can need.


ለመሣቅ (ከአብራሃም ዘ.)
***********************************************************************

.
……....ታዲያ እንዲሁ ሡርቶ ራሱን ለማስተዳደርና ድሃ ቤተሰቦቹን ለመርዳት ይጓጓ የነበረ ወጣት አበሻ ጸሎቱ ሰምሮ እዚሁ ጣሊያን ይመጣል:: ለመስራት ካለው ጉጉት የተነሳ ጣሊያንን ከረገጠበት ቀን ጀምሮ በተለያዩ ከተሞች እየሄደ ሥራ ማፈላለጉን ተያያዘው:: ዕድሉ አልቀና ብሎት ለረዥም ግዜ ያለሥራ መቀመጥ በመገደዱ ይጨነቅ ጀመር::
ይህንን ጭንቀቱን ያየ አንድ ጣሊያናዊ ለጎብኚዎች መዝናኛ ተብሎ የተሠራ የዱር አራዊት የሚገኙበት ቦታ (zoo) ሄዶ ሥራ እንዲያገኝና እንዲሞክር ይነግረውና እዚሁ ጣሊያን ሀገር በምትገኘው pistoia የምትባለው ከተማ ይሄዳል:: "zoo di pistoia" ውስጥ ገብቶም ሥራ አላችሁ ወይ ብሎ ይጠይቃል:: በአጋጣሚም ምንም የሥራ ልምድ የማይጠይቅ የግማሽ ሰዓት ሥልጠና ብቻ የሚያስፈልገው ሥራ ያገኛል::
……....ሥራውም የዱር አራዊት ምስል ማስኬራ (maschera) አጥልቆ በብረት አጥር ውስጥ ገብቶ እንደተመደበበት እንሰሳ መሆን ነው:: አጅሬም በአጋጣሚ የተመደበው እንደ ጎሬላ ዝንጀሮ ሆኖ እንዲሠራ ነበርና የተሰጠውን የ30 ደቂቃ ስልጠና በብቃት አጠናቆ እንደ ዝንጀሮ መንጎማለል፣ መጮህ፣ መፈናጠር፣ ብቻ ምን አለፋችሁ ሁሉን መሆን ችሎ ወደ ሥራው ተሰማራ:: ጠዋት ሄዶ እስከ ማታ በብረት አጥር ውስጥ ሲንጎማለል ውሎ ማታ ወደ ሰውነቱም ወደቤቱም ይመለሳል:: ረዥም ሰዓት ስለሚሠራና ክፍያውም ጥሩ ስለሆነ በአጭር ግዜ ውስጥ ይጓጓለት የነበረውን ሁሉ በእጁ ማስገባት በመቻሉ ጭንቀቱ ወደ ፈጹም ደስታ ተለውጠ:: ሥራውንም ተላመደው::
……....ታዲያ መቼም በየቀኑ ለ12 ሰዓት ከአራዊት መንጋ ጋር መዋል ቀላል አይደለም:: ከዚያ አለቃውም ጉብዝናውን አይቶ ስለተደሰተ ብር ጨምሮ ሰጠው። ይህቺን ሰርቼ ብር ከተጨመረልኝማ ሌላም ነገር ሰርቼ የበለጠ አገኛለሁ አለና በማግስቱ መገለባበጥ ጀመረ። አጅሬውም ሲገለባበጥ ሳያስበው አንበሶች ያሉበት ወስጥ ተገልብጦ ገባ። አንበሶቹን እንዳያቸው ደንግጦ "እመ ብርሀን ከዚህ ጉድ አውጪኝ አለቀልኝ" እያለ በልቡ ሲያወራ ወዲያው የውስጡ ሠራተኞች የሆኑት ቶሎ ብለው ገብተው ወዲያው ይለያይዋቸዋል።
……....ታዲያ አራዊት ያው አራዊት ነውና ሳት ብሎ የሾለከ ቀን አያድርስ ነው:: አጅሬም ያው እንደገና የፈራው አልቀረም አንድ ቀን በአንበሳውና በሱ መካከል ያለው በር ሳይዘጋ ተረስቶ ኖሮ አያ አንበሴ ጎልመም ጎልመም እያለ ወደ እሱ መጣበት። አጅሬም ዝንጀሮነቱን እረስቶ "ወይኔ ጉዴ ወይኔ ምነው በቀረብኝ" እያለ በጭንቀት የሚገባበት ጠፍቶት አንዱ ጥግ ብረት ላይ ይለጠፋል:: አፉን አውጥቶ እንዳይጮህ ጎብኝዎች ስላሉ ተቸግሮ በጭንቅ ውስጥ እንዳለ ሳያስበው "ገብርኤል አውጣኝ" ሲል አንበሳው አማርኛ ሲናገር ጊዜ ቆም ብሎ "እንዴ! አበሻ ነህ እንዴ? "ብሎት እርፍ:: አንበሳ ከመቼ ጀምሮ ያወራል ብሎ ሲደነግጥ ለካስ አያ አንበሴዎቹም የኛው ሰዎች ነበሩ::
- ድሮስ ለአንበስነቱ ማን ብሎን!!
- ዝንጀሮነቱም ቢሆን የእንእጀራ ነገር ሆኖ እንጂ::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም ዘ.) ***********************************************************************
.
አንድ ሚላኖ የሚኖር አበሻ ነው እናትና አባቱን ካገርቤት አስምጥቶ ከተማውን እያዞረ ያሳያቸው ጀመረ:: ታዲያ ወደ የግድግዳዉ ብቻ ጠጋ እያለ በbancomat ይኼንን euro ከግድግዳው ሲያስፈተልክ ያዩታል:: አባትዬው ግድግዳው ሁሉ ገንዘብ ሲተፋ አይተው በጣም ተገርመውና ተደንቀው ይሰነብታሉ:: ሳምንታት ያህል ቆዩና ወደ አገርቤት የመመለሻቸው ቀን ደረሰና እሳቸውን በመሸኘት ላይ እንዳለ ከአንዱ ግድግዳ ተጠጋና 500 euro አውጥቶ "ይህንን ለኪስዎ ብዬ ነው" ብሎ ይሰጣቸዋል::
አባትየውም በጣም አዝነው "ምነዉ ልጄ ዝም ብሎ ከየግድግዳው ዝም ብሎ ለሚብዋተተዉ ነፈግ ነፈግ የምታደርገው ለማን አስበህ ነዉ?" አሉ ይባላል::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም ዘ.) ***********************************************************************
.
"እግዜር ሆይ!! እንደው ምናለበት totocalcio እንዳሸንፍ ወይም ሎተሪ እንኳን እንዲደርሰኝ ብታደርግ" እያለ ሁልግዜ በማማረር የሚጸልይ አበሻ ነበር:: ቤተክርስቲያን አንድም ቀን ሳያቋርጥ እየደጋገመ በመሄድ ፀሎቱን እያለቀሰ ተያያዘው:: ታዲያ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ማልቀስ የተለመደ አይደለም:: እናም የቤተክርስቲያኑ parrocco ሁልጊዜ ማልቀሱን አይተው ያሳዝናቸውና እግዜርን... "ይህ ሰው ሁልግዜ እየመጣ ይጸልያል:: ስምህንም እየጠራ ያለቅሳል:: ታዲያ ምን አለበት ጸሎቱን ብትሰማለት? ምኞቱን ብታሳካለት?" ይላሉ:: እግዜርም መልሱን ሲሰጣቸው "ሁልግዜ እየመጣ እንደሚጸልይ አውቃለሁ:: ታዲያ እኔ ምንላድርገው? መጀመሪያ totcalcioውን ይጫወታ!!!" አላቸው ይባላል::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም ዘ.) ***********************************************************************
.
ሁለት carabinieri አንዱን አበሻ መንገድ ላይ ያስቆሙትና documento አሳየን ቢሉት
- አበሻው - "የለኝም"
- soggiornoህን አውጣ ሲሉት
- አበሻው - "እሱም የለኝም"
- "ፓስፖርትህን አሳየን"
- አበሻው - "እሱም የለኝም"
carabiniereው እንዴት አርጎ እዚህ አገር ያለመረጃ ሊኖር ይችላል ብሎ ያው CPT ክመወሰዱ በፊት ልምርመራ ቀርቦ እንዲጠየቅ ተድረገ።
carabinieri - "እድሜህ ስንት ነው?"
አበሻ - "28" ይላል::
carabinieri - "እርግጠኛ ነህ?"
አበሻ - "ቆይ ላስብበት" ይልና ቆይቶ " 28 አይደለም ተሳስቼ ነው። 24 ማለቴ ነበር" ይላል::
carabinieri - "ግን እርግጠኛ መሆን አለብህ" ሲባል
አበሻ - "አሁንም ላስብ ጊዜ ስጡኝ" ይልና "20" ይላል:: እንዲህ እያለ እየወረደ ቢያስቸግራቸው አንዱ ከሳሽ carabinieriው ብድግ ይልና "ክቡር giudice ሆይ! እኔ የምጠይቀው ነገር ቢኖር ይሄ ሰውዬ ተመልሶ ወደ እናቱ ማህጸን ከመግባቱ በፊት ያለው እድሜ ይመዝገብልኝ" አለ ይባላል::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም ዘ.) ***********************************************************************
.
እዚህ ይኖር የነበረ አበሻ ለሁለት ዓመት ሶጆርኖ ጠብቆ ስላላገኘ ትንሽ በአእምሮ በጨጭ አርጎት ጓደኞቹ ግንዝብ አዋጥተው ውደ ሀገር ቤት ይልኩታል። ከእዚህ ከላኩት ጓደኞች አንዱ ከወራት በኋላ ወደ ቤተሰቦቹ ጤንነቱን ለማወቅ ብሎ ስልክ ይደውልና ከእናቱ ጋር ሲያወራ ...
ስልክ ደዋይ - "ተሻለው ወይ?"
እናትዮው - "እድሜ ለእናንተ ጓደኞቹ:: ተጋግዛችሁ ባትልኩልኝ ኖሮ ልጄ በስው ሀገር ሞቶ ይቀር ነበር"
ስልክ ደዋይ - "አይ! እዚህ እኮ መተዛዘን መረዳዳት የተለመደ ነው:: እንኳን ይሄ ቀርቶ ሌላም ይደረጋል"
እናትዬው - "ግን እኮ ወዲያው እንዳመመው ብትልኩልኝ ኖሮ በጣም ይድን ነበር" ሲሉት ጊዜ
ስልክ ደዋይ - "አይ እማማ ወዲያው እንደታመመ ይላክ ከተባለማ ጣሊያን ውስጥ ያለው አበሻ ሁሉ ይላክ ነበር" አላቸው::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም ዘ.) ***********************************************************************.
.
ሮማ ከተማ ለgay matrimonio ድጋፍ በወጡ በብዙ ሺህ በሚቆጠሩ ግብረሰዶሞች መሐከል አንዱ ሀበሻ የሀገራችንን ባንዲራ ከፍ አርጎ ይዞ እያውለበለበ ከፊት ረድፍ ሆኖ ሰልፉን ይመራል:: በዚህም ብቻ ሳይወሰን አጅሬው ሌሎቹ የሚሉትን መፈክር ቀደም ቀደም እያለ ድምጹን ከፍ አርጎ ያስተጋባል። ይህንን የአዩና የተበሳጩ አበሾች "ይህ የኛው ጉድ አይደል" ብለው ...
"አንተ ስማ! እንዴት የአገራችንን ባንዲራ ይዘህ ከomosesuale ጋር ሰላማዊ ሰልፍ ተወጣለህ? ቢሉት ...
"ሞኛችሁን ፈልጉ! ለgay መጋባት ከተፈቀድላቸው ደስታዬን አልችለውም" ...
"ታዲያ እነሱ ስለተጋቡ አንተን ይህን ያህል ያስደስተሃል እንዴ?" ...
"እንዴታ!! እኔም ወንድሜን አግብቼ ከኢትዮጵያ አስመጣው ነበር" ... ብሏቸው አረፈው::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ሴትየዋ ልጆቻቸውን ለመጠየቅ ጣሊያን ይመጡና በዚሁ ቀርተው ጣሊያን መኖር ከጀመሩ ዓመት አለፋቸው:: በጠና ይታመሙና ሆስፒታል ገብተው ትንሽ ጊዜ ብቻ እንደቀራቸው ሀኪሞች ቁርጡን ነገርዋቸው። ያው እንግዴ ከመሞታቸው በፊት አንድ ቀን ልጆቻቸው እንዲህ ብለው ይጠይቋቸዋል:: እማዬ ድንገት ከሞትሽ የት እንቅበርሽ? እዚሁ ጣሊያን ውይስ ኢትዮጲያ ይሻላል? ብለው ሲጠይቁቸው እናትዬውም "አይ ምነው ልጆቼ! ያው ስሞት ሶርፕሬሳ (sorpressa) ብታረጉኝ" አሉዋቸውና ቁጭ::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
እናት ከአዲስ አበባ በተዘዋዋሪ ስልክ ሚላኖ ለሚኖረው ልጃቸው ደውለው ሲያወሩ ቆይተው
ልጅም ለቤተሰቦቹ ጤንነት ጠይቆ ሲያበቃ "ምነው እማዬ በደህና ደወልሽ ወይ?" ብሎ ቢጠይቃቸው
እናት ፡-"አይ ልጄ ትንሽ ገንዘብ ቸግሮኝ ነው"
ልጅ ፡- እንዳልሰማ መስሎ "አይሰማኝም ስልኩ ብልሽት አለው መሰለኝ" ብሎ ሲመልስ
ኦፐሬተሯ ፡- በመሃል ገብታ "ገንዘብ ላክልኝ ነው የሚሉህ" ብትለው
ልጅ ፡-"ዝም በይ! ደደብ! ታዲያ ገንዘብ አንቺ ካለሽ ስጫት" ብሎ ስልኩን ዘጋው::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
እናት ከሀገር ቤት በስልክ ጣሊያን ለምትኖረው ልጃቸዉ "እዚያ እናንተ ጋ erboristeria የሚባል ሱቅ ውስጥ ወጣት የሚያደርግ መድሀኒት አላቸው ይባላል:: እንዲያዉ ፈልገሽ ላኪልኝ" ብለዉ ሲያስጨንቋት ጊዜ ፈልጋ ፈልጋ በ pillola መልክ የሚዋጠውን ገዛችላቸውና ላከችላቸው:: በኋላም ስልክ ደዉላ "እማዬ ያልሽዉን ልኬልሻለሁ:: አወሳስዱም በቀን አንድ ብቻ ነዉ:: በምንም አይነት መንገድ ከአንድ በላይ እንዳትወስጂ" mi raccomando ብላ ታስጠነቅቃቸዋለች:: እንደተባሉትም መጠቀም ይጀምራሉ:: መድሀኒቱ እየሰራ የእናትየውን ወዝ እንደገና ሲመጣ ያዩት አባት "እኔም ይህን ኪኒን ካልዋጥኩ" ብለዉ ያስቸግሩ ጀመር:: እናት አወሳሰዱን አስረድተዉ አባትም ከመድሀኒቱ መዉሰድ ይጀምራሉ:: ከዓመታት በኋላ ልጃቸው ሀገር ቤት ስትመጣ ኤርፖርት ሊቀበልዋት ከመጡት ሰዎች መሀል እናትዋ የሀያ አመት ወጣት መስለዉና ልጅ አዝለው ጠበቋት:: የመድሀኒቱ መስራት እየገረማት እናትዋን ከሳመች በሁዋላ "አባዬስ?" ብላ ጠየቀች:: እናትም "አይይ እሱማ የላክሽልን ኪኒን አንድ አንድ ብቻ ነዉ የሚወሰደዉ ብዬ ብነግረዉ አልሰማ ብሎ አራት አራት እየዋጠልሽ ይኸዉ አዝዬዉ መጥቻለሁ" ብለዉ ያዘሉትን ማሙሽ አሳይዋት::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
አንድ በችግር ላይ ያለ ሰው በጣሊያን ካለው ዘመዱ እርዳታ ፈልጎ ደብዳቤ በተደጋጋሚ ቢጽፍ መልስ አያገኝም:: በኋላም የሚለኝን ከቃሉ ለስማ ብሎ እንደምንም ብሎ ገንዘብ ተበድሮ ስልክ ይደውልለታል። በስልክ እንዳገኘውም ችግሩን ዘርዝሮ ነግሮ የሚለብሰው ሱሪ እንኳን ከቂጡ የተቀደደ መሆኑ ቢነግረው "ሱሪህ መቀደዱን ለምን ዞር ብለህ ታያለህ" አለው ይባላል::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
አባት ገጠር ሆነው ጣሊያን ካለው ልጃቸው ጋር በስልክ እያወሩ ነበር:: ግን ልጃቸው የአባቱን ድምጽ መስማት ተስኖት ስለነበር "አባዬ ድምጽህ አይሰማም ምንድነው ስልኩ ችግር አለው?" ብሎ ቢጠይቅ አባትም "አይ ልጄ! እንደዉ በሽታ ቢጤ ቢይዘኝ ነጭ ሽንኩርት በላሁና አፌ እንዳይሸትህ ብዬ ተሸፋፍኜ ነው የማናግርህ" ብለው ቁጭ::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
እኛ አፍሪካውያን እንዴት እንደምንኖር አንዳንድ ጣሊያኖች በደንብ አያውቁም። እናም አንድ ጣሊያናዊ አንዱን አበሻ ይተዋወቅና እንዲህ ብሎ ጠየቀው::
ጣሊያናዊ :- አፍሪካ ውስጥ እናንተ የምትኖሩት በዛፍ ላይ ነው አይደል? ብሎ ጠየቀው::
አበሻውም በንዴት "አዎ" አለው::
ጣሊያናዊ :- እንዴት ነው ዛፉ ላይ የምትወጡት?
አበሻውም :- "በ ascensore" አለው ይባላል::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ሴት ልጃቸውን ለመጠየቅ የመጡ እናት ናቸው አሉ:: ታዲያ ማታማታ ሲተኙ ከልጃቸው እና ከባለቤቱዋ መኝታ ቤት ውስጥ የሚሰሙት የማቃሰት ድምጽ ያሳስባቸዋል:: ታዲያ አንድ ቀን ምን ሰይጣን ነው እንዲህ የሚያረጋቸው ብለው ለማረጋገጥ ፈራ ተባ እያሉ ወደ ልጃቸው ምኝታ ቤት በዝግታ ይጠጋሉ በሩ በደንብ አልተዘጋም:: በቀዳዳ ያያሉ:: ደነገጡ :: ወደመኝታቸው ተመለሱና በማግስቱ ጠዋት ወዲያው ወደአገር ቤት ስልክ ደወሉ::
እናት - ሀሎ ደህና ሰነበታችሁ
ስልክ መላሽ - ደህና ነኝ
እናት - ሁሉን ስመጣ እናወራለን::
ስልክ መላሽ - ምኑን?
እናት - እረ ተውኝ::
ስልክ መላሽ - ምን ተፈጠረ?
እናት - አይ ይ ይ ይ!!!! "ልጄ ጥጃ ሁናለች" አሉ ይባላል።
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ሴትየዋ ጣሊያን ብዙ ጊዜ ከርመው አገር ቤት በተመለሱ በሳምንቱ እድርተኛቸው የሆነ ሰው ስለሞተ ቀብር ለመድረስ ተቻኩለው ሰራተኛቸውን "ማነሽ እስቲ! ከበቡሽ! " ያንን ነጠላ አቀብይኝ እባክሽ!
ከበቡሽም ንጠላውን ስትፈልግ ስትዘገየችባቸው ጊዜ
ሴትዮዋ ይናደዱና አንቺ ልጅ ያንን cazzo ነጠላ አምጪልኝ ለቅሶ ደርሼ ልምጣ ቶሎ በይ ብዬሻለሁ።
አሁንም ስትዘገይብቸው ግዜ ይቺ ባፋንኩሎ ሶርዳ " ያሉትን የሰማ አለ?
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
አበበ ቢቂላ እዚሁ ጣሊያን ሮማ ውስጥ ባለው stadio olimpico ውስጥ በባዶ እግሩ ማራቶን ያሸነፈ ጊዜ አንድ የተሸነፈ ሯጭ "ለምን በባዶ እግሩ እንዲሮጥ ፈቀዳችሁለት?" "እሱ እኮ ያሸነፈው ሸክም ስለቀለለት ነው" ብሎ ክስ በማቅረብ ዳኞቹን ሲጠይቃቸው ጊዜ ምን ብለው መለሱለት መሰላችሁ? "አንተም ሸክም እንዲቅልልህ ከፈለግህ ለምን ራቁትህን ሮጠህ አታሸንፍም ነበር?" ብለው መለሱለት ይባላል::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
አንዱ እዚሁ ጣሊያን ሀገር ሆኖ እጮኛው ከሀግር ቤት ደብዳቤ ጻፈችለት:: "ከእንግዲህ ብኋላ የኔና ያንተ ነገር እዚሁ ላይ ቢያበቃ ይሻላል:: ከሌላ ልጅም ፍቅር ይዞኛል:: ደግሞም እስከዛሬ ድረስ የላኩልህን ፎቶግራፎቼን ቶሎ መልስልኝ" አለችው:: እሱም በጣም ይናደድና ወደ ጓደኞቹ ሄዶ እነሱ የማይፈልጓቸውን የሴት ፎቶግራፎች ሰብስቦ "መልክሽ ስለጠፋኝ ከነዚህ ፎቶግራፍ መሀል ምረጪና የራስሽን ወስደሽ ሌሎቹን እንድትመልሽልኝ አደራሽን" ብሎ ጻፈላት::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ሚላኖ የሚቀመጥ ለቤተሰቦቹ ስልክ እንኳን ደውሎ የማያውቅ ከብዙ ዓመት በኋላ ቤተሰቦቹን ለመጠየቅ አገር ቤት ሄደ። ቦሌ ኤርፖርት ሲደርስ አሽከር ተቀበለው። ከአሽከሩም ጋር እንደተገናኙ ስለቤተሰቦቹ ይጠይቀው ጀመረ።
አሽከርየውም "ሁሉ ደህና ናቸው ብቻ ..." ብሎ ዝም አለ።
ልጅዬውም "ምነው ምን ተፈጠረ?"
አሽከር "ትልቁ ውሻ ሞተ"
ልጁ - "ምን ሆኖ?"
አሽከር - "እሱማ የትልቁን በሬ አንጀት ሲጎትት ታንቆ ሞት"
ልጅ - "በሬውን ምን ነካው?
አሽከር - "በሬውማ ለእሜቴ አርባ ታረደ እኮ!"
ልጅ - በጣም ይደነግጥና "እማዬ ምን ሆና ሞተች?"
አሽከር "እሳቸውማ በጌቶች ሞት አዝነው ሞቱ" ብሎ ቁርጡን ነገረው።
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ባላገር የሚኖሩ አባት ሮም የሚኖረውን ልጃቸውን ለመጠየቅ እዚህ ከፉሚቺኖ aeroporto እየወጡ እያለ እቺ ጠጋ ሲሏት የምትከፈት የመስታውት በር ታጋጥመዋለች:: ሻንጣውን ቁጭ ያደርጉና ሊከፍቱ ጠጋ ሲሉ ክፍት ይላል:: እሰይ ብሎ ሻንጣ ሊያነሱ በሚመለሱበት ጊዜ ተመልሶ ይዘጋባቸዋል:: አሁንም ለመክፈት ሲመጡ እራሱ ይከፈታል:: ወደ ሻንጣው ሲመለሱ አሁንም ዝግት ሲልባቸው በንዴት ወደ ስዉ ይዞሩና "ጎበዝ ይሄ ምን ይቀልዳል?" ብለው ጠይቀው ነበር ይባላል::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ጋሼ ከበደ ቡና ቤት ሲገባ ሁል ጊዜ 3 ቢራ በአንድ ጊዜ እያዘዘ ነው የሚጠጣው:: እንደጨረሰም እንደገና በሌላ ዙር 3 ቢራ ያዝና ይጠጣል። መጠጥ ቀጂውም "ለምንድነው 1 ቢራ ከማዘዝ 3 ቢራ በአንድ ጊዜ የምታዘው?" ብሎ ሲጠይቀው ጋሼ ከበደም "አይ! ሁለት ጓደኞቼ ወደ ውጪ ሀገር ስለሄዱና ስለተለያየን ያው መጠጥ ስንጠጣ ለሶስተችንም እያዘዝን እንድንጠጣ ቃል ስለተገባባን ለዚህ ነው በየዙሩ 3 የማዘው" አለው:: እነሱም መጠጥ ሲያዙ እንደዚሁ ነው። ጋሼ ከበደም ብዙ ጊዜ እየተመላለሰ ደንበኛ ሆነ:: ታዲያ አንድ ቀን ወደ ቡና ቤት ይገባና 2 ቢራና 1 ለስላሳ ያዛል:: መጠጥ ቀጂውም "ምነው ዛሬ ቀየርክ?" ቢለው እሱም መልሶ "እኔ መጠጥ ትቻለሁ" አለው:: menomale ለስላሳ ማዘዙ! almeno ሁለተኛ ዙር ብሎ አይደግምም። እነዚያ የተከፈቱት 2ቱ ቢራዎች ግን አያሳዝኑም!! ይታያችሁ እንግዲህ!! ያው ወደ ጋሼ ከበደ ጠጋ ማለት ሳያዋጣ አይቀርም
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
አንዷ አበሻ ለቢሮ ሥራ ለመቀጠር ወደ አንድ cooperativa ትሄድና ከሥራ ቀጣሪው ጋር ስለሥራው እየተነጋገረችና ጥያቄ እየተደረገላት ነበር...
ቀጣሪው - "ደሞዝ ስንስት ቢከፈልሽ ጥሩ ነው?"
ተቀጣሪዋ - "2000 ኤውሮ" አለች::
ቀጣሪው - "እንደውም 3000 ኤውሮ እናደርግልሻለን፣ ደግሞም አንድ ወር የዓመት ፈቃድ ከአዲስ መኪና ጋር ቢስጥሽ ምን ይመስልሻል?" አላት::
ተቀጣሪዋ - ደንግጣ "ቀልድዎን ነው አይደል?" ብትለው
ቀጣሪው - "አይ! ቀልዱን እኮ የጀመርሽው አንቺ ነሽ" አላት::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ጣሊያን ሀገር የሚኖር ዜግነቱን ግን ወደ ጣሊያናዊነት የለወጠ አበሻ ከ fiumicino ተነስቶ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ከሻንጣ ፈታሾቹ ጋር አለመግባባት ይፈጥርና በሚሠሩት ስዎች ላይ ስለ ውጭ አገር ዜጋነቱ ይደነፋል:: ታዲያ ምን እንዳደረጉ ታውቃላችሁ? ዝም አሉና ልጁ የሚያርፍበትን አድራሻ ተቀብለው በሰላም ሸኙት:: ከዚያም እቤቱ ሄደው "በል በኢትዮጵያ ህግ መሰረት አንድ የውጭ ዜጋ ሌላ ሰው ቤት ማረፍ አይችልም":: ይህም ለውጪ ሀገር ዜጎች የተለየ ጥበቃና protection ደግሞም ለአንተ security ሲባል ከጸጥታ አንጻር ችግር እንዳይገጥምህ ተብሎ ነው:: ከዛ በኋላማ ምናለፋችሁ ጊዜውን በሙሉ ......
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ጋሼ ከበደ እድላቸው ሆኖ አሜሪካ ገቡና ኑሮን ሲኖሩ sex ሳያደርጉ ብዙ ጊዜ ሆኗቸው ነበር:: ታዲያ አንድ ቀን አንድ ሁለት ተባብልው ይሳካላቸውና አንዷን አበሻ ይዘው እቤታቸው ይዘዋት ይመጣሉ:: ወደ አልጋ ይሄዳሉ ...
ታድያ ጋሼ ከበደ አሷን ከላይ አርገው አሳቸው ከታች ሆነው ፍቅር እየሠሩ ነበር:: ልጀትዋም ከላያቸው ሆና ጸጉርዋንም ስትሠራው ነበር:: ጋሼ ከቤም የምታደርገውን አዩና ከልባቸው ተበሳጭተው ..."ምን አያደርግሽ ነው?" ብለው ሲጠይቋት አሷም ስትመልስ "አሜሪካ እኮ ሁለት ሥራ ካልተሠራ መኖር አይቻለም" አለቻቸው ይባላል::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
አንድ ሰውዬ ለስራ ጉዳይ ወደ ውጭ ሲሄድ ለቅርብ ጓደኛው የሚስቴን ነገር አደራ:: ችግር ካለም ፃፍልኝ ብሎት ሄደ:: ከትንሽ ሳምንት በኋላ እንዲ ብሎ ፃፈለት
ውድ ወንድሜ :-
1ኛ ) በጣልክብኝ አደራ መሠረት ባለቤትህን በየጊዜው እጠይቃታለሁ። በጣም ደህና ናት::
2ኛ ) ከብዙ ወንዶች ጋር ተዋውቃለች። እናም ሲያወጧት አይቻለሁ::
3ኛ ) እኔንም አሳስታኝ አውጥቻታለሁ::
4ኝ ) ስለ 3ኛው ጉዳይ ምን አስተያየት አለህ ?
ባልየውም ይህ ደብዳቤ እንደደርሰው እንዲህ ብሎ መለሰለት
ውድ ጓደኛዬ :-
1ኛ ) ደብዳቤህ ደርሶኛል አመሰግናለው::
2ኛ ) ባለቤቴን ብዙ ወንዶች እና አንተም እንዳወጣሀት ገልፅህልኛል::
3ኛ ) ባለቤቴ ግን የሚጋባ በሽታ አለባት::
4ኛ ) አንተስ ስለ 3ኛው ጉዳይ ምን ትላለህ ?
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
የፈረንጅ ባህል ይዞ የተምታታበት አበሻ አገርቤት ለእረፍት ሄዶ ሳለ አንድ ቀን የታመመ ዘመድ ከጠየቀ በኋላ ሊሰናበት ሲል "በሉ እንግዲህ ወደሩቅ አገር ስለምሄድ ለቀብር አይመቸኝም" የሞተ እንደሆነ እናንተንም እግዚአብሔር ያጽናችሁ አላቸው ይባላል
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ብዙ ዓመት እዚህ የተቀመጠ አበሻ ሀገር ቤት እየሄደ ሚስት በማግባት ከአንዴም ሁለቴም ሶስስቴም እዚህ አስመጥቷል:: ነገር ግን ያመጣቸው ሚስቶች ትንሽ ወሮች ተቀምጠው ጥለውት ስለሚሄዱ በቃ ያለሚስት ተቀምጧል:: እናም አንድ ይህንን ችግሩን ያልየ አበሻ "አንተ ለምንድነው ሚስት የማታገባው?" ሲለው እሱም "አንተ ይህን አታውቅም እንዴ? እዚህ የሀገራችን ሴት ሁሉም የተያዘ ነው:: ያለኝ ተስፋ ያ በየግዜው ሚስት ከሀገር ቤት የሚያስመጣውን ዘዴ እየተጠቀምኩ እኮ ነው። አሁን ደግሞ 4ኛ ሚስት ለማስመጣት በፕሮሰስ ላይ ነኝ" አለው ይባላል::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ሶስት (3) ሰላዮች ይመረጡ ተባለና ኢትዮጲያዊ፣ ጣሊያናዊ፣ እንግሊዛዊ የዘመኑ ስላይ በመባል ተመረጡ። ከ እነሱም ውስጥ እስቲ ማነው የበልጠ ፈታንና ቀልጣፋ ተብሎ ፍየል አምጡ ተብለው ሲላኩ
እንግሊዛዊው - ወዲያው ከች አደረገ
ጣሊያናዊው - በንጋታው ከች አረገ
ኢትዮጲያዊው - ስድስት ቀን ቆይቶ አፍዋ ደም በደም የሆነች ውሻ ከች ሲያደርግ "ምንነካህ አንተ?" ሲባል አይ በቃ አምናለች እኮ አለ:: (ውሻዋን ደብድቦ ፍየል ነኝ ብላ አሳምኗታል)
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
አዛውንቱ ጣሊያን ሀገር ብዙ ነገር አይተዋል:: ካዩዋቸው ነገሮች በጣም የወደዱት ቢኖር ግን የባለጊውን ፊልም ነው:: ታዲያ አንድ ቀን ፊልሙን በጥሞና እየተክታሉ ሳለ አንዷ ትመጣና እንዴ! አባባ! እርስዎ ትልቅ ሰው አደሉ እንዴ? ይህን የባለጌ ፊልም ያያሉ? ስትላቸው ባአባባሏ የበሸቁት አዛውንት "ዝም በይ! ምላሰኛ! ምላስ እዚህ ስንት ቁም ነገር ይሠራበታል መሰለሽ:: አንቺ ግን ዝም ብለሽ ታወሪበታለሽ" አልዋት ይባላል::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ሮማ ውስጥ ካሪታስ የሚመገቡ ሁለት ጓደኛሞች ሁልግዜ ምግብ ለመብላት በተራ በተራ ነው። የሚሄዱት እና ቀድሞ የበላው ምን እደሆነ የሚነግረው በምልክት ነው።
ያልበላው ፡- ምን ነበር ዛሬ?
በልቶ የመጣው ፡- "ዳ" ነው ይለዋል።
ያልበላው ፡- አሀ ዳቦ ነው ማለት ነው ይልና እሱም ሊበላ ይሄዳል።
በሌላ ቀን ያልበላው ፡- ዛሬስ ይለዋል
በልቶ የመጣው ፡- "ፓ" ነው ይለዋል
ያልበላው ፡- ፓስታ ማለት ነው። ብሎ ሊበላ ይሄዳል
በሶስተኛው ቀን ያልበላው ዛሬስ ሲለው
በልቶ የመጣው ፡-"ዝ" ነው ይለዋል
ያልበላው ፡- ደንግጦ ዝልዝል ተደርጎም አይታወቅም ብሎ ሲሮጥ ይሄዳል እዛም ሲደርስ ዝግ ነው ለካስ። "ዝ" ያለው ዝግ ማለቱ ነው
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
አንድ አባት ልጃቸውን ለመጠየቅ ጣሊያን ይመጣሉ:: ከዚያም ልጃቸው ሁሉግዜ ማታ ማታ ጥላቸው ወደ ውጭ እያመሸሽ ትመጣለች::
ይህንን ያዩ እና በሁኔታው የተቆጡ አባት "ልጄ ሆይ! ምነው ማታ ማታ ልክ እንደሀገሬ ሰካራም ሰው እያመሸሽ ትገቢያለሽ ጥሩ እኮ አይደለም" ሲሏት
ልጃቸውም "አባዬ ይህ እኮ አውሮፓ ነው:: ልትቆጣጠረኝ አትችልም" አለቻቸው::
ይህንን የሰሙ አባት እምምምም... ብለው ልጃቸውን ከጠየቁ ከወር በኋላ ወደ አዲስአበባ ተመለሱ:: ከዚያም ከአንድ ዓመት ብኋላ ደግሞ ልጃቸው ወደ ኢትዮጲያ ትሄዳለች:: ማታ ማታ ዙረት የለምደች ልጅ አምሽታ ቤት ስትገባ አባቷ ልክ እንደገባች በጥፊ ያልሷታል:: ከዚያም ጥፊ የቀመሰችው ልጅ አባቷን ምነው አባዬ ምን አደርኩ በጥፊ መታሃኝ ስትላቸው አባትም "ይሄ እኮ ኢትዮጲያ ነው" አሏት ይባላል::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ልጆቻቸውን ለመጥየቅ ሮማ የመጡ ሁለት እናቶች አውቶቢስ ፌርማታ ጋ ይገናኛሉ:: አንዷ 5 ቁጥር አውቶቢስ ስትሆን ወደቤት የምትወስዳቸው የአንድኛዋ ደግሞ 8 ቁጥር አውቶቢስ ነበር የምትወስዳቸው:: እና አጋጣሚ ሆኖ 58 ቁጥር አውቶቢስ ትመጣለች:: ሴቶቹ አቤት መታደል ሁለታችን የምትወስድ አውቶቢስ በአንድ መጣችልን ይሉና ተሳፍረው ጥፍት አሉ:: ያው ቀኑን ሙሉ ብዛው አውቶቡስ እየዞሩ እያለ ያቺ አምስት ቁጥር የምትጠብቀዋ ረዥም ፎቅ አይታ ፎቁን ትቆጥር ጀመር:: 1 - 2 - 3 - 4 ... ሲቆጥሩ የሰማ አንድ ጩልሌ መጣና "ስንት ቆጠሩ?" ብሎ ጠየቃት:: "15" ብላ መለሰች:: ጩልሌው ሂሳብ አወራረደና 2 ኤውሮ ላንድ ፎቅ! 15 ፎቅ ስለቆጠሩ ሰላሳ ኤውሮ ይክፈሉ!" ብሎ ዓይኑን አጉረጠረጠባቸው:: እሷም "እሺ እሺ ብላ ከፍላ ተገላገልችው:: በኋላ ጓደኛዋን "ሸወደኩት እኮ!" አለቻት:: ጓደኛዋ "እንዴት?" ብላ ስትጠይቃት እሷም "25 ፎቅ ነበር የቆጠርኩት"
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ኢትዮጲያ ውስጥ ገጠር ትኖር የነበረች አንዲት ልጅ ጣሊያን ሀገር መጣችና አንድ ቀን አስቤዛ ለማድረግ ወደሱፐር ማርኬት ወጣ አለች። ከዚያም ገባችና የምትፈልገውን ነገሮች መፈለግ ጀመረች። ይህች ሰው በአይምሮዋ ያለውን ነገር ፈልጋ ማግኘት አልቻለችም ነበር። ከዚያም ገራ ተጋብታ ሳለ አንዱ ሠራተኛ ምን እያደረገች እንድሆነ ግራ ተጋብቶ ሲጠይቃት የምትፈልገውን እቃ በጣሊያንኛ ቋንቋ ማውቅ ስላልቻለች እጁን ጎትታ ወስዳ እንቁላሉን በእጇ ይዛ "dove la madre di questo uovo?" ብላ ቁጭ።
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
አንዱ ገና ከአገርቤት እዚህ ጣሊያን እንደመጣ ለጭፈራ ከጓደኞቹ ጋር ወጥቶ "እባካችው እኔ ፈረንጅ መቅመስ እፈልጋለሁ እንደምንም አገናኙኝ" አላቸው:: እነሱም "እራስህ ሞክር አትፍራ" አሉት:: እሱም ፍለጋውን ተያይዞ ከአይናችው ተሰውሮ ያገኘውን ይዞ ሄድዋል:: ስሟም ሮዛ (Rosa) ነበር የምትባለው:: ታዲያ አልጋ ላይ ይዝዋት በሆድዋ ተኛችበት:: ከዛ እሱም ስራውን ይቀጥላል:: መብራት አጥፍቶ ስለነበር ሆድዋን እይዛለው ብሎ ከፊት ያለውን እቃዋን ይይዛል:: ከዛ ደንግጦ "ሮዚ በሳሁሽ ወይኔ በሳሁሽ" ማለት ለካስ ሮዚ ወንድ ኖርዋል::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
አንዱ በቅርቡ ጣሊያን ህገር ይመጣና ልክ በ1ወሩ 100 ኤውሮ ወደ አገርቤት ላከና አባቱን በል አባዬ ወደ ኢትዮ ብር ሲለወጥ 1000 ብር ይሆናልና አንድ ነገር አድርግበት አላቸው:: በ3ኛ ወሩ ሲደውል አባቱ ምነው ልጄ የት ጠፋህሳ?
አባዬ እኔ ያለሁበት ከተማ ውስጥ የመሬት መንቀጥቀጥ ስለደረሰ ነው ይጠፋሁት።
አባትዬውም እህ የሞተና የተጎዳ ሰውስ አለ?
ልጃችውም አዎ 100 የሚሆኑ ሞተዋል
አባትዬውም ስለዚህ ወደእኛ ሲቀየር 1000 ሰው ሞቷል ማለት ነው?
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************
.
ዘበርጋ ማይክል ክሚባል ጛደኛው ጋር አሪዞና ውስጥ የሚገኘውን የግራንድ ካንየን ሽለቆ ለመጎብኘት ይሂዳል። ታድያ ሽለቆዉን በመጎብኘት ላይ እንዳሉ ማይክልን እየውልህ እንግዲህ አሁን ድምጺ ከፍ አድርገ ስሜን ብጣራ የገደል ማሚቶው ስሜን 10 ጊዜ ይደጋግመዋል ይለዋል ለዘበርጋ:: እንዳለውም ጮክ ብሎ ማይክል ሲል ሸለቆዎም ተከትሎ .. ማይክል.. ማይክል.. ማይክል.. አለ:: ይህን የተገነዝበ ዘበርጋም ለምን ታድያ እኒም አልሞክርም ይልና እሱም በተራው ጮሆ ዘበርጋ ብሎ ሲጮህ ግራንድ ካንየኑ ምን ብሎ መለሰለት መሰላችሁ "I beg your pardon?" ብሎ መለሰለት::
.
ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************

አንዱ ክላንዴስቲኒ የአንገት ሀብል ቀምቶ በማምለጥ በጣም የታወቀ ነው። ይሄ ልጅ በጣም ስላስቸገረ ፖሊስ አንድ ማስታወቂያ አወጣ። ይህም ማስታወቂያ የሚለው፡- "በዚህ አካባቢ የምትኖሩ ሴቶችም ሆናችሁ ወንዶች እባካችሁን ግድ ካልሆነባችሁ በስተቀር አርቴፊሻል የአንገት ሀብል አድርጉ።" በእርግጥም ይሄ ማስታወቂያ ከወጣ በኌላ ሰላም ሆነ። የዚህ ጭልፊት ልጅ ገበያም ስለቀነሰ ሙሉ ትኩረቱን የእጅ ስልክ ላይ አዞረ። ታዲያ አንድ ቀን አንድ አባት የእጅ ስልካቸውን ይዘው ሲያወሩ ያስተውልና ግራ ቀኙን አየት አየት አድርጎ ከኌላቸው መከተል ይጀምራል። እኝህ አባት የዚህን ልጅ ዝና ሰምተው ስለነበር ወዲያውኑ እንዳዩት የሚያወሩትን ሰው እንኴን "ደህና ዋል" ሳይሉ ስልካቸውን ዘግተው ኪሳቸው ውስጥ ያደርጉና መንገዳቸውን ይቀጥላሉ። በዚህ ጊዜ ስልክ ኪሳቸው ውስጥ ሆና መጮህ ጀመረች። አባት ደግሞ እየሰሙ ዝም። አሁንም ትንሽ ቆየና ስልክ ጮሀች። እሳቸው ምናቸው ሞኝ ነው "እሲኪ ትፈነጂ እንደሆነ አይሻለሁ" ብለው ዝም። ለሶስተኛ ጊዜ ስልክ ጮሀች። በዚህ ጊዜ አጅሬ ከኌላቸው ሆኖ "አረ -ፋዘር! ስልክ ይጮሀል። ምናልባት ኢመርጀንሲም ሊሆን ይችላል የዛሬ ነገር እኮ አይታወቅም" ቢላቸው ሰውየውም መለስ አሉና" አይ የኔ ልጅ ግድየለህም ተውው እኔ ከምጮህ እሷ ብትጮህ ይሻላል።

. ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)

******************************************

ከሃምሳ ዓመታት በፊት ወደ ጣልያን ተጉዞ ፓስታ እየበላ የቆየ መምህር ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ ስለ ምግብ ሲያስተምር “ምግብ ማለት ከሱፐር
ማርኬት የሚገዛ፣ የሚቀቀል፣ ስጎ የሚጨመርበት፣ ከዚያም በሹካ የሚበላ ማለት ነው” አለና ተማሪዎቹን አስተማረ፡፡ ከዚያም ተማሪዎቹን አንድ ነገር ጠየቀ “እንጀራ ከሱፐር ማርኬት ይገዛል?” “አይገዛም” አሉት፡፡ “እንጀራ ይቀቀላል”? “አይቀቀልም” “ስጎ ይጨመርበታል”?
“አይጨመርበትም” “በሹካ ይበላል”? “አይበላም” “እንግዲያውማ እንጀራ ምግብ አይደለም ማለት ነው” አላቸው ይባላል፡፡

. ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)

******************************************




አለሚቱ ከሀገርቤት ወዲያውኑ እንደመጣች ሰው ቤት ተቀጠረች። ቀጣሪዎችዋም እስቲ ወጣ ትበል ብለው ለመጀመሪያ ሙከራ ሱቅ ላኳት። ያው 5 ኤውሮ ሰጥተዋት “uovo” በይና እና እንቁላል ግዢ አሏት። ትንሽ እንደሄደች ጠፋባት። ለባለ ሱቁ በምን ትናገር? ለካ ቀጣሪዎቿ ለሀገሩ አዲስ ስለሆነች እንዳትጠፋ ብለው ከሁዋላ እየተከተሏት ነበር። እሷ ለባለሱቁ ለማስረዳት ግራና ቀኝ እጁን እያማታች “ኩኩ” ብላ ከሁዋላ የምትጥለውን ለማሳየት ያረገችውን እንቅስቃሴ አይተው ሳቃቸውን መቆጣጠር አቃታቸው።

. ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************



ወይዘሮ ጌጤ እድሜ ጠግበው፣ የልጅ ልጅ አይተው፣ ለማንም የማይቀረው ሞት እሳቸውንም ይዞ ሊሄድ ባልጋቸው ዙሪያ መዞር ጀመረ:: እስቸውም ያቃስታሉ። ዙሪያቸውን ልጆቻቸው የልጅ ልጆቻቸው የቅርብ ዘመድ እንዲሁም ለክፉም ለደጉም ቢሆን የሚናዘዙትም ካለ ተብሎ የነፍስ አባታቸውም ተገኝተዋል::
"እኅኅኅህ ....አረ ወይኔ! አይ ዘንድሮ! ባጭር ተቀጨሁ! አየዬ! አይ ሰው መሆን!!!" አሉ ጌጤ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ውስጥ ሆነው::

"አይዞሽ እማማ ምንም እኮ አትሆኚም" አለ ቾምቤ እያሉ የሚጠሩትና ከልጅ ልጆቻቸው ውስጥ በጣም የሚያቀርቡት አንዱ ልጃቸው::
"አዬ ቾምብዬ ተወኝ የኔ ነገር እማ በቃው ....ይሀው የናንተን .. የናንተን መጨረሻ እንኴን ሳላይ ይህው ተቀጠፍኩ:: ባጭር ቀረሁ" እንደ ማልቀስ ቃጣቸው::
ሁኔታውን በጽሞና ይከታተሉ የነበሩ የነፍስ አባታቸው ጊዜው አልፎ ነገሮች ከመቀየራቸው በፊት ደብተርና ኢስክሪፕቶ ይዘው ጠጋ አሉና "አይ ወለተ ወልድ አይዞኦ ....እመ -ብርሀን አቅፋ ደግፋ ልጇን እንዳሸገረችው እርሶንም በቅፏ ታሻግርዎታለች በርታ ይበሉ ደግ አይደለም እንደዚ ሲሆኑ ጻድቃን ይቀየማሉ ደስ አይላቸውም" ብለው ከተቆጣጧቸው በኌላ ....
"ይበሉ አሁን የሚናዘዙትን ይንገሩኝና በማስታወሻዬ ላይ ልጣፍ::" አሉ አባ ሞት እንዳይቀድማቸው በመስጋት::
"እሺ አባቴ በነጥብ በነጥብ ይያዙልኝ እንግዲህ::" ጌጤ ራሳቸውን እንደምንም ቀና አድርገው ወደ ነፍስ አባታቸው እያዩ መናዘዝ ጀመሩ ::
"ይጻፉ አባቴ::"
1. "ባንካ ዲ ሮማ 10000 ኤውሮ"
"እሺ አስር ሺህ" ቄሱም ጻፉ::
2. "ባንካ ዲ ላቮሮ 7000 ሺህ"
3. "ባንካ ዲ ኢታሊያ አስራአምስት ሺህ"
"ደግ ነው ወለተ -ወልድ! እንዴት ይከፋፈል ታዲያ?" አባ ጠየቁ::
"እዳዬ ነው ልጆቼ:: ያልጨርስኩት እዳ ነው:: ክፈሉት::"

. ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)

******************************************

ወይዘሮ ቀለሟ ልጃቸው ዳዊት በላከላቸው የግብዣ ወረቀት አስፈላጊውን የጉዞ ፎርማሊቲ ጨርሰው ወደ ጣሊያን ሊያቀኑ ቀን ቀርቷቸዋል:: ከገጠር ካመጧት የቤት ሰራተኛቸው ተናኘ ጋር እየተጋገዙ ድርቆሹን በሶውን በርበሬውን ሚጥሚጣውን ዳቦ ቆሎውን ምጥኑን ባይነት በመልክ በመልኩ እያደረጉ ሻንጣ ውስጥ ያስገባሉ:: ሁኔታቸውን ላየ ቀለሟ ጣሊያን የሚመጡ ሳይሆን ሊሸፍቱ በረሀ የሚገቡ ይመስላሉ:: የፈረንጅ በረሀ:: በዚህ መሀል ስልክ ተደወለ:: ደዋዩ ልጃቸው ዳዊት ነው::
"ምነው ልጄ ትናትና ደውለህ አልነበር ምን ችግር አጋጠመህና ዛሬ ደወልክ?" አሉ ቀለሟ::
" አይ እማዬ ቡዙ ነገር አትያዠ ሁሉም እዚህ አለ ሸክም እንዳታበዠ ብዬ ነው::"
"አይ የኔ ልጅ ታዲያ የኔ የእናትህን እጅ የሚያስበልጥ አለ እንዴ? እኔ እናትህ እንኴን ላንተ ለሌላም እተርፋለሁ አይዞህ አታስብ ቡዙም ነገር አልያዝኩ::"
"ጥሩ ነው እሺ እማዬ እንዳልሽው ይሁን... ብቻ አንድ ነገር ልንገርሽ....!!" አለ ዳዊት ልቡ ፈራ እያለ::
"ምንድነው ልጄ የምትነገረኝ" አሉ ቀለሟ ለመስማት ቸኮሉ::
"ይህእውልሽ እማዬ መቼም የጣሊያን ሀገር ኑሮ ውድ ስለሆነ የቤት ኪራይና አንዳንድ ወጭ እንድታግዘኝ ብዬ አስገብቻለሁ ::
"አግብቻታለሁ!!ማናት ደሞ እሷ?"
"ኖ ኖ እማዬ ደባል የምትሆነኝ ልጅ ማለቴ ነው:: የመብራቱንም የስልኩንም የውሀንም ኪራይ እየተካፈልን አብራኝ የምትኖር ደባል አለችኝ:: ከመምጣትሽ በፊት እንድታውቂው ብዬ ነው::"
ቀለሟ ነገሩ ቡዙ አልጣማቸውም:: "ከሴት ልጅ ጋር ደባልነት! እንዴት እሺ አለችህ ልጄ እንደው ያለ ፊርማም ያለ ወረቀትም ዝም ብላ ገባችልህ ማለት ነው?"
"አይ እማዬ እንደምታስቢው አይደለም እዚህ ስትመጨ ሁሉንም ነገር ታይዋለሽ:: ግኑኝነታችን ምንም ሌላ መልክ የለውም:: ለመረዳዳት ስንል ብቻ ያደረግነው ነው::"
ወይዘሮ ቀለሟ መልሱ ቡዙ ባያረካቸውም በልባቸው "ስመጣ ሁሉንም አይ የለ" ይሉና ልጃችውንም ላለማስደንገጥ ብለው "እሺ ይሁንልህ" ብለው ወደ ጣሊያን ያቀናሉ:: በርግጥም ሁሉ ነገር ለየብቻ ነው:: ልጃቸው ዳዊትና ደባሏ ማህሌት የሚተኙት በተለያየ ክፍል ነው:: ሁለቱም የራሳቸው የመታጠቢያ ቤት አላቸው:: በጋራ የሚጠቀሙት ማድቤቱንና የሳሎኑን ቤት ብቻ ነው:: ይሁን እንጂ የሁለቱ ባንድ ቤት ውስጥ መኖር ስሜታቸው ቡዙ ሳይወደው የእረፍት ጊዜአቸውን ጨርሰው ወደ ሀገራቸው ይመለሳሉ:: በተመለሱ በሳምንቱ አንድ እሁድ ቀን ማህሌት ቡና ልታፈላ ቤቱን እንደ ባለ ትዳር ቤት ሞቅ ደመቅ ልታደርገው ፈልጋ ጀበናውን ብትፈልግ አጣችው:: ያልገባችበት ቦታ የለም ቤቱን ከዳር እስከ ዳር አሰሰችው:: ካገር ቤት በስንት ልመና ሰው አስቸግራ የመጣችው ጀበና ደብዛው ጠፋ:: እየቆየች ስትሄድ አንድ ክፉ ሀሳብ በአእምሮዋ ውስጥ መመላለስ ጀመረ::
"እንዴ ምናልባት ጀበናዬን የዳዊት እናት ወስደውት ቢሆንስ ? ወይ ጉድ የሚገርም ነው!! የሄዱት ኢትዮጵያ ምን አጥተው ነው የኔን ጀበና ይዘውብኝ የሚሄዱት?"
ጉዳዩ በጣም ስላበሳጫትም ስላስገረማትም ለዳዊት ነገርችው:: ዳዊት መጀመሪያ ነገሩን አላመነም::
"ሁሉም ጋ ፈልገሽ አጣሽው ማለት ነው?" አላት ለናቱ ምን ብሎ በስልክ እንደሚጠይቃቸው እያሰበ::
"ያልፈልኩት ቦታ የለም መቼም መርፌ አይደል" አለችው ማህሌት ፍጥጥ ብላ እያየችው::
ዳዊት ሲፈራ ሲቸር እናቱ ጋ ስልክ መታ::
ስለጤንነታቸውና አጠቃላይ ነገሮችን ከጠያየቃቸው በኌላ ቀልድ መሆኑን ለማሳወቅ ሳቅ እያለ.....
"እማዬ እንዴት ነው የቡና ጀበናችንን ይዘሽብን ሄድሽ እንዴ? ፈልገን እኮ አጣነው ...."አለ እየሳቀ::
"አጣችሁት?" አሉ ወይዘሮ ቀለሟ በምጸት::
"አዎ እማዬ ማህሌት ያልፈለገችበት ቦታ የላትም ቤቱን ከዳር እስከ ዳር አስስዋለች::
"በል የኔ ልጅ ስማኝ ይሀውልህ እቺን እቤትህ ያለችውን ኮማሪት እንዲህ በልልኝ::
"ምን ልበላት?" ዳዊት የልቡ ምት እየጨመረ ሲመጣ ታወቀው::
"ስሚ ምነው አልጋሽ አስጠላሽ በልልኝ.... ምነው እንደ ፌንጣ ካልጋ አልጋ ትዘያለሽ በልልኝ::"
"አረ እማዬ ምን እያልሽ ነው?" ዳዊት ግራ እየገባው ጠየቀ::
ወይ የኔልጅ ይልቁኑ እኔ እናትህ የምነግርህን በደንብ ስማና ንገርልኝ::" አንቺ መቁሊያ እግር በልልኝ::"
አረ እማዬ የምትይው ምንም አልገባኝም:: እኔ እኮ የምጠይቅሽ ስለጀበናው አንቺ ደግሞ የምታወሪው..... እያለ ሲቀጥል ቀለሟ በመሀል አቌረጡትና "አይ ልጄ እኔም የምነግርህ ስለ ጠፋው ጀበና ነው:: "ይልቁኑ ሰሞኑን ደውልልኝና እኔና አባትህ አንተን ራስህን ለጥብቅ ጉዳይ ልናነጋርህ እንፈልጋለን" ብለው ወይዘሮ ቀለሟ የዳዊት እናት ስልኩን ይዘጉታል::
ወይዘሮ ቀለሟ ወደ ኢትዮጵያ ለመሄድ የተነሱ ዕለት ማህሌት መኝታ ቤት ገብተው ጀበናውን በጥንቃቄ አመቻችተው ትራሷ መሀል ማስቀመጣቸውን ግን ማንም አላስተዋለም ነበር::

ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)

******************************************


ከኢትዮጲያ ወደ ጣሊያን ለመምጣት በዝግጅት ላይ ነች:: ሁሉ ነገር ተጠቃሎ ይዛ የምትሄደው ሁሉ መኪና ውስጥ ከተጫነ በኌላ ጉዞ ወደ ቦሌ ይጀመራል:: በጉዟቸው ላይ እያሉ ከጎኗ ለተቀመጡት አባቷ
ልጅ = "መቼም አባብዬ በሰላም እዛች ሀገር ልግባ እንጂ ቀንም ማታም ሰርቼ የመጀመሪያ ፕሮግራሜ መጦሪያህ የሚሆንህን ታክሲ እልክልሀለሁ:: የዛ ሰው ይበለኝ እንጂ::"
አባት = "አይ የኔ ልጅ አንቺ ሰላምና ጤና ሁኚልኝ እንጂ ይደርሳል:: ይሄንን ማሰብሽ እራሱ እንዳደረግሸው እቆጥረዋለሁ" አሉ በልጃቸው ኩራት እየተሰማቸው::
ዐመታት አለፉ:: ቃል የተገባላቸው ታክሲ የውህ ሽታ ሆነ:: በዚህ መሀል አንድ አስገራሚ ነገር ተከሰተ:: ልጃቸው አንድ ያልታወቀ ቦዘኔ ወዳ አስወልዷት ያለበትን አድራሻ እንኴን ሳይነግራት ጥሏት ስለጠፋ የሚረዳት ስላጣችና ከስራ ጋር ስላልትመቻት በሁነኛ ሰው ልጇን ላባቷ ትልካለች:: ያልጠበቁት እንግዳ የመጣባቸውም አባትም መገረምም መደነቅም ይዟቸው ለልጃቸው ማስታወሻ ጽፈው ሰደዱላት::
የኔ ልጅ እንዴት ሰነበትሽ? ደህና ነሽ ወይ? ምነው ልጄ ታክሲው ሳይመጣ ወያላው ቀደመ?

.
. ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)

******************************************

ልጅ ጣሊያን ሀገር ውስጥ ኑሮውን ከጀመረ ጥቂት አመታትን አስቆጠረ:: ታዲያ ከኑሮ ውድነት ጋር የራሱም ንፉግነት ተጨምሮ ቀብቃባ እንዲሆን አድርጎታል:: ለቤተ ሰቦቹ እንኴን ሲደውል ጤንነትቻውን ለማወቅ ካልሆነ በስተቀር ስለሌላ ጉዳይ አያነጋግርም:: አንድ ቀን ሲደውል አባቱን አገኘ::
አባት: "እንዴት ነህ ደህና ነህ? ምነው ልጄ እንዲህ ትጠፋብናለህ ? እንደው እኮ ዝም ብለህ ስትጠፋ እኔም እናትህም ተጨነቅን::"
ልጅ: አባዬ ምን ላድርግ ብለህ ነው! ኑሮው እነደምታየው አስቸጋሪ ነው አይመችም:: ለዛ ነው:: በል አባዬ ዋናው ድምጽህን ከሰማሁ ይበቃል:: ይቆጥርብኛል" ይልና የአባቱን ይሁንታ ሳይጠይቅ ስልኩን ጆሯቸው ላይ ይዘጋል::
በሚቀጥለው ጊዜ ሲደውል እናቱን ያገኛል::
እናት: "ሀሎ ምነው ልጄ እንዲህ ጨከንክ? ሰው እንኴን አትናፍቅም?"
ልጅ: "ምን መሰለሽ እማምዬ አልመች እያለኝ እኮ እንጂ እኔማ ማሰቤ እኮ አልቀረም::"
እና: "እሺ ይሁና እኔማ ይሄ ልጅ ላመት ባሉ እንኴን ...ብለው ሳይጨርሱ የነገሩ አዝማሚያው የገባው ልጃቸው ፈጠን አለና "እማዬ ስልኩ ይቆጥርብኛል ሌላ ጊዜ በሰፊው አወራሻለሁ" ይልና ስልኩን ጆሯቸው ላይ ዝግት:: ይሄ ነገር ያሳሰባቸው እናትና አባት አንድ ቀን እቤት ተቀምጠው ሲወያዩ
እናት: "አንቱዬ እንዴት ነው ነገሩ ልጃችን እንደው የልባችንን ሳያናግረን እንደው ናፍቆታችንን እንኴን ሳንጨርስ ጆሯችን ላይ ስልኩን መዝጋቱ ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው?"
አባትም ሁኔታው ቢያሳስባቸውም ሚስታቸውን ለማጽናናት ሲሉ "አይ አይዞሽ አትዘኚ አመሪካን እንዲህ እንደኛ ሀገር አይደለም ዝም ብሎ ስልክ አይመታም:: ልጃችንም ያዝልቅለት እንጂ በዚህ ከቀጠለ ጥሩ የውሀና የመብራት ቆጣሪ ይወጣዋል" አያሉ ሚስታቸውን ሲያጽናኑ ስልክ ጮኽ:: ያው ልጃቸው ነው:: ስልኩን አባት ያነሱና
አባት: "ልጄ ሰላም ነህ ጤናህስ ደህና ነው?" ይሉታል::
ልጅም "ደህና ነኝ አባዬ ይህውልህ እንደውም ዛሬ እኛ ጋ በአል ስለሆነ ስራ የለም አንተንም እማዬንም በደንብ አወራችኌለሁ::
አባትም ደስ እያላቸው "ቀጥል እስኪ ልጄ"
ልጅ: ይኸውልህ አባዬ እዚህ አገር ውጭ እየሄዱ ምግብ መብላት በጣም ሰልችቶኛል:: በዚህ ላይ ምግባቸው ጤነኛ አይደለም:: ካሁን በኌላ ራሴ እየሰራሁ ለመብላት ወስኛለሁ:: ስለዚህ ከማዬ ጋር ተነጋገሩና 3 ኪሎ በርበሬ 3 ኪሎ ሚጥሚጣ አንድ 5 ኪሎ ቅቤ በሶ አንድ ሶስት ኪሎ የሚሆን ጭኮ 5 ኪሎ የኤልሳ ቆሎ ከተመቸ ደሞ ክሽን ተደርጎ የተሰራ ዶሮ በፍሪዝ አቀዝቅዛችሁ .....እንዲሁም አልጫ ....እያለ ሊቀጥል ሲል አባት ቀበል አደረጉና
"ልጄ የኔ ልጅ ቆይ ስማኝ ይሄንን ሁሉ ስታወራ እኮ ስልኩ ይቆጥርብሀል አሉትና ጆሮው ላይ ድርግም::

ለመሣቅ (ከአብራሃም.ዘ)
******************************************

የጎረቤት ሴቶች ተሰብስበው ስለልጆቻቸው ወግ ሲያወጉ "የኔ ልጅ ያለችው ጣሊያን፣ ፈራንሳይ፣ አሜሪካ፣ ካናዳ ነው" እያሉ ሲጫወቱ አንደኛዋ ብድግ ብላ "የኔ ደግሞ ያለችው ጅቡቲ ነው" ስትል አንዷ ብድግ አለችና "ምን ውጭ አገር ትያለሽ ጓሮ ነው ያለችው አትይም እንዴ!" አሏት ይባላል::

******************************************


አንዱ አበሻ ልጅ ዋና ለመማር piscina ይሄድና ሲዋኝ ይሰምጥና መውጣት ያቅተዋል። ከዚያ እዚያው ውሀ ውስጥ እየተንፈራገጠ በአጠገቡ ሰው እንዳለ ሲመለከት አንድ ጠና ያሉ ሰውዬ በpiscinaው አጠገብ ሲያልፉ ያያል። የሰጠመውም ልጅ "አባባ aiutare! ... Io morire! ... እያለ ሲጮህ ሰውዬው ደግሞ ዞር አሉና እንዲህ አሉት " ጣሊያንኛ ከመማርህ በፊት ዋና አትማርም ነበር?" አሉት።
Endale T/Mariam (Roma)

******************************************




ኢትዮጵያዊው ተገደለ

08 02 2010


……....ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ 06 2 2010 ከጠዋቱ 10 ሰዓት ላይ በሚላኖና በቤርጋሞ መካከል በምትገኘው የትሬቪሊዮ የባቡር ጣቢያ ሀዲድ ላይ የአንድ ኢትዮጵያዊ አስከሬን ተጋድሞ ተገኘ። ለመጀመሪያ ግዜ አስከሬኑን ያየው በጣቢያው ደራሽ በሆነ ሌላ ባቡር ላይ ተጓዥ የነበረ ግለሰብ መሆኑንና ይኸውም ግለሰብ ወደፖሊስ ጽህፈት ቤት ሄዶ ሊያሳውቅ በመቻሉ ነው። ሟቹም ዳንኤል ተፈራ የተባለ የ36 እመት እድሜ ያለው ነው።

……....ፖሊስ የራሱን ክትትል አድርጎ ግድያው በሰው እንደተፈጸመበት መረጃዎች ሊያገኝ መቻሉን ብዙ የዜና አውታሮች ገልጸዋል። አስከሬኑ ሲገኝ ህይወቱን ያጣው ከ3 ሰዓት በፊት እንደነበር ሊደረስበት ተችሏል። የተገደለበት ሰዓት በየሳምንቱ ቤርጋሞ የምትገኘውን ዘመዱን ለመጠየቅ በሚሄድበት የንጋት ሰዓት ላይ ነው። ግድያውን የፈጸሙትን ለማግኘት ፖሲስ ማጣራቱን እንደሚቀጥል ቢናገርም እስካሁን ከተለያዩ መላምቶችና ግምቶች ሌላ ምን ሁኔታ ላይ እንደተደረሰ የሚታወቅ ነገር የለም። የወንጀል ምርመራ ማጣሪያው እንደሚቀጥል በመጪውም ማክሰኞ (09 02 10) ላይ የኦቶፕሲ ውጤት እንደሚወጣ ቃል ሰጥተዋል።

……....ቤርጋሞ ውስጥ የምትኖረው ዘመዱ እስራኤል የምትባል ሲሆን ይህንን አስደንጋጭ መልዕክት እንደሰማች ወዲያው በቦታው ለመድረስ ችላለች። በቦታውም ላይ እንደተገኘች በሁኔታው ላይ የመረረ ተማጽኖ አሰምታለች። "አስከሬኑ ሶስት ሰዓት ሙሉ ማንም ሳያየው ባቡር ሀዲድ ላይ ታንጋሎ ያረፈደበት ምክንያትስ ለምን ይሆን? ሌላው ደግሞ በባቡር ጣቢያው ላይ የመቆጣጠርያ ቪዲዮ ማንሻ የሌለበት ምክንያት ለምንድነው?" ብላ ቅሬታዋን በመግለጽ ሀቁን ለማወቅ ትሻለች። በአካባቢው ከተገኙት ወገኖቹ ደግሞ "ዳንኤል ባልታሰበ ሁኔታ ህይወቱ ተቀጥፎና ሀዲድ ላይ ተጥሎ ስለመገኘቱ አሳዛኝና በሁላችንም ላይ የተቃጣ ጥቃት ነው" ሲሉ አስተያየት ሰጥተዋል።

……....ዳንኤል የተወለደው አዲስ አበባ ሲሆን 11 ዓመት ሲሞላው ከነቤተሰቡ ወደ አስመራ ተዛውሮ እስከ 2006 ዓም ድረስ ኖርዋል። ጣሊያን ከመጣ 5 ዓመት እንደሆነ፣ የመኖሪያ ፈቃድ ያለው ግን እስከሚታደስለት የሚጠብቅ መሆኑን ከልዩልዩ ዜና አውታሮች ዘገባ ላይ የተወሰዱ ሪፖርቶች ያመለክታሉ። በሀገሩ ሚስትና የ 9 አመት ያላት ልጅ አለው። ስዊድን ውስጥ ደግሞ ሶስት እህቶች እንዳለውና በቅርቡም ሊመጡ እንደሚችሉ ታውቋል።

……....ከዚህ በታች በሰው ለመገደሉና በባቡር ያለመገጨቱ ማረጋገጫ ሊሆኑ የሚችሉት ማስረጃዎች ሰፍረዋል። 1ኛ/ ከአስከሬኑ አጠገብ አንድ የብረት ቅዝምዝም የመገኘቱ ጉዳይ ይህም በደም የተበከለና ክጭንቅላቱ ቁስል ጋር ያሚያገናኝ የምርመራ ፍንጭ ስለአለው፣ 2ኛ/ በጭንቅላቱ ላይ ከተገኘው ቁስል ሌላ ሰውነቱ ላይ የመጎሳቆል ምልክት አለመኖሩ ይኸውም አስከሬኑ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ያልተዘዋወረና ያልተጎተተ መሆኑ፣ 3ኛ/ አስከሬኑ የተገኘው የ5ተኛው የባቡር መስመር (ቢናሪዮ) ላይ ተጋድሞ መሆኑና ይኸውም ሊወስድ ከሚችለው ባቡር መስመር በጣም የራቀ በመሆኑ 4ኛ/ የዳንኤል ዘመድም "በየሳምንቱ ሲመጣ በፑልማን እንጂ በባር እንዳልሆነ ሲመጣም በቀጥታ ወደእኔ እንጂ ትሬቪሊዮ ሊወርድ ወይም ባቡር ሊቀይር የሚችልበት ምክንያት ያለው አይመስለኝም" ብላ ስላረጋገጠች፣ ...ወዘተ... የመሳሰሉት ሁሉ በሰው ለመገደሉ ተጨማሪ ማስረጃዎች ሊሆኑ ይችላሉ።

አብራሃም ዘውዴ (ቦሎኛ)


ማስታወሻ ……....ምርመራው ከተጠናቀቀ በኋላ ሀገርቤት ያሉት ቤተሰቦቹና ዘመዶች አስከሬኑን እንዲያገኙና እንዲቀብሩ መሆን አለበት። በዚህ ረገድ ከአለፉት ልምዶች በመነሳት ማንም የሚደርስልን ስለሌለ (መንግስትም ቢሆን እጁን የማይሰጥ፣ የእኛም ኤምባሲ ቢሆን እንደምናውቀው ስለሆነ) አስከሬኑን ወደ ሀገሩ ለመላክና ለመሸኘት እንዲሁም የቀብር ሥነሥርዓቱን ለማስፈፀሚያ በሚደረገው ትብብር ላይ በአካባቢው የምንገኝ ወገኖች የእርዳታ እጃችን እንዘረጋ። እንዲሁም የቅርብ ቤተሰቦቹ በድንገት በመጣው ሀዘን ምክንያት ችግር ላይ እንዳይወድቁ ጥቂት መስዋትነት መክፈል የሚቀጥለው ተግባራችን ይሁን። እዚህም የሚቀበር ከሆነ በተለመደው የመደጋገፍና የመተዛዘን ልምዳችን እንቀጥልበት።

ለዳንኤል ተፈራ ቤተሰቦች፣ ዘመዶች፣ ጓደኞችና ወዳጆች ሁሉ በያሉበት መጽናናትን እንመኛለን። አምላክ ነፍሱን በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍልን፡፡ የኢትዮጵያ በጣሊያን (ethiopiainitaly.com) ዝግጅት ክፍል


L'autopsia conferma etiope ucciso


con un colpo in testa


……....Teferi, il 35enne trovato morto la mattina del 6 febbraio sul binario numero 5 della Stazione Centrale di Treviglio, è stato ucciso: l'autopsia eseguita martedì - che pure non ha sciolto i dubbi su cosa sia avvenuto - ha comunque confermato che la ferita presente sulla fronte è compatibile con una provocata da un gesto violento e che sul corpo della vittima non ci sono altre lesioni che possano far pensare a lesioni di altre organi vitali. Sul fronte delle indagini non ci sono novità, ma ormai la pista degli inquirenti si è indirizzata verso quella dell'omicidio. ……....Intanto sono emersi alcuni particolari sulla vita di Daniel Teferi.L'uomo era nato ad Adis Abeba, ma all'età di 11 anni si era trasferito ad Asmara, in Eritrea, dove ha vissuto fino al 2006, anno in cui è venuto in Italia. In Eritrea, ha lasciato la mamma, la moglie e una figlia di nove anni. ……....Daniel Teferi viveva a Bergamo con una cugina, Israel, 33 anni, barista in un locale pubblico di Milano. E proprio con la cugina, Daniel aveva trascorso la serata di sabato in un bar di Porta Venezia a Milano: lei aveva bevuto un caffè, lui una birra. "Mi sembrava il solito Daniel di sempre - ha raccontato la donna agli amici -, tranquillo, senza particolari preoccupazioni. Ha detto che avrebbe dormito da amici a Milano e che la mattina presto sarebbe rientrato a Bergamo. Di solito prendeva il pullman, non capisco come mai questa volta abbia preso il treno e sia finito alla Stazione Centrale di Treviglio". ……....Fino a qualche mese fa, Daniel Teferi - in Italia con regolare permesso di soggiorno. Aveva lavorato come elettricista per una ditta di Lecco, ma attualmente era disoccupato. In Europa, Teferi aveva altre tre sorelle, che attualmente vivono in Svezia. ……....Sabato mattina la polizia scientifica del commissariato trevigliese aveva sequestrato una spranga in ferro, sporca di sangue, lunga un metro, con un diametro di 5 centimetri e sulla sommità ha una base quadrata larga 12 centimetri: si tratta di una parte di uno dei pali che vengono utilizzati proprio nei cantieri per costruire le impalcature.

Sequestrati gli indumenti


15 02 2010

…….... Alcuni amici di Daniel Teferi attendono di sapere l'esito dell'autopsia. Potrebbe essere rimpatriata presto la salma di Daniel Teferi, l'eritreo trentacinquenne di origine etiope trovato morto la mattina di sabato 6 febbraio lungo il binario 5 della stazione centrale di Treviglio. Il magistrato titolare delle indagini ha infatti dato il via libera alla restituzione della salma ai familiari, che nei giorni scorsi avevano fatto sapere di essere intenzionati a riportare in patria il corpo per i funerali. …….... Lunedì, però, a quanto riferito dai familiari, non era stata ancora stabilita la data del rimpatrio. Nel frattempo la Polfer, che sta portando avanti le indagini sotto il coordinamento della procura di Bergamo, ha posto sotto sequestro gli indumenti che l'africano indossava quando è stato trovato morto: il provvedimento è stato preso per consentire ulteriori accertamenti scientifici alla ricerca di eventuali tracce biologiche lasciate dall'aggressore. …….... Tra la vittima e il suo assassino, infatti, c'è stata una colluttazione (nell'autopsia sono stati rilevati dei tagli da difesa sulle mani dell'etiope) e nello scontro potrebbero essere rimaste tracce di sangue o di saliva, da cui estrarre il Dna. L'uomo, stando a quanto emerso sempre dall'autopsia, era stato ucciso con un oggetto pesante (forse una pietra o un mattone) con cui è stato colpito una o due volte alla testa. …….... Inizialmente si era ipotizzato che le ferite fossero state inferte con un bastone, trovato vicino al corpo e sequestrato, ma dall'esame medico legale è emerso che le ferite non sono compatibili con quell'oggetto. Per ora non risultano esserci indagati nell'inchiesta sull'omicidio. …….... Gli investigatori hanno ascoltato familiari e conoscenti della vittima per ricostruire i suoi spostamenti nelle ore precedenti all'omicidio e chiarire se il trentacinquenne avesse dissapori con qualcuno. Risalire al movente, infatti, è un passaggio fondamentale per individuare i potenziali sospettati. …….... Dell'omicidio, avvenuto secondo le prime ipotesi verso le 7 della mattina di sabato 6 febbraio (il corpo è stato trovato verso le 10), non ci sarebbero testimoni.


በጣሊያን የዘር መድሎ የአደባባይ ሚስጥር...

………በጣሊያን በመጨረሻዎቹ ሳምንታት ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የጸረስደተኛ እና የዘር መድልዎ ክስተቶች ታይተውባታል። ለምሳሌ የ”White Chrismas” በኮካሊዮ (Coccaglio) አገረግዢ የ ”caccia all’immigrato” መፈክር አዝሎ ዘመቻ፣ በስታዲዮሞች ውስጥ የዘር ጥላቻ ዝመራ ወዘተ… ይገኙበታል። ………በተለይም የዛሬ ሳምንት በአፍሪቃዉያን ላይ ስለተፈፀመዉ በደል በተለያዩ የዜና ምንጮች የሰሞኑ ርዕሰአንቀፅ ሆኖ ቆይቷል። ይኸውም ሬጆ ካላብሪያ አውራጃ በምትገኘው የሮዛርኖ ከተማ የተቀሰቀሰው የጸረ ስደተኞች ዘመቻ የሚያወግዙ ዜናዎች ናቸው። የዚህች ከተማ ነዋሪዎች ለሰላማዊ ሰልፍ በተሰባሰቡ አፍሪቃዉያን ላይ ሲዘምቱ በተነሳዉ ግጭት በርካታ አፍሪካውያን ሊቆስሉ ችለዋል። ከግጭቱ በሕዋላ በፍርሃትና በድንጋጤ በሺሕ የሚቆጠሩ አፍሪቃዉያን ከአካባቢዉ ሸሽተዋል። በዚህች ሀገር የዘር መድሎዎች እንደምከስትና የአደባባይ ሚስጥር መሆኑን አሁንም በድጋሜ ተረጋግጧል። ………እነዚህን የጸረ ስደተኛ እና የዘር መድልዎ በተለያዩ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ከመወገዛቸው ሌላ ጉዳዩ ምን ያህል አሳሳቢነት እንደአለው በግልጽ አስምረውበታል። ከእነዚህ የመብት ተሟጋች ድርጅት አንዱ (HRW) የሮሳርኖ ግዛት የሰብዓዊ መብትን እንደተጋፋችና ስደተኞችን ያለፍላጎታቸው በማፈናቀሏ ብዙ እንደወቀሳት ከዜና ማሰራጫዎቻቸው መረዳት ይቻላል፡፡ ………የጣሊያን መንግሥትም እነዚህን ተፈናቃዮች በጊዜያዊ የሰፈራ ማቆያዎች (CPT) ውስጥ እያጠራቀሙአቸው ወይም ደግሞ በተለያዩ የ(CIE) Centri di Identificazione ed Espulsione በመበታተንና በማሰራጨት ጊዜያዊው የመኖሪያ ፈቃዱ የወደቀባቸውንና የሌላቸውን በአጭር ጊዜ ውስጥ ያለውዴታቸው ወደመጡበት የሚመልስበትም ሁኔታ አለበት። እነዚህንም ወደየሀገራቸው ከመለሱአቸው ደግሞ በመብታቸው፣ በሕይወታቸው የሚደርሰው ስጋት፣ ከሀገራቸው የሕገ-ወጥ እሥራት፣ ግርፋትና የአስገዳጅ ውትድርና፣ ከሌሎችም ተጽዕኖዎች ወዘተ ሁሉ ማምለጥ እንደማይችሉ (HRW) በሪፖርቱ ይፋ አድርጓል። ብዙዎቹን በያሉበት ስለበታተኑዋቸው ለዘረኛ አራማጆች እና እያቆጠቆጡ ለመጡ የፋሽስት ርዝራዦች የተጋለጡ ሆነው ይገኛሉ። እንደገናም በተለያዩ የፖለቲካ አክራሪዎችና የወንጀል ቡድኖች በስውር ታፍነው መልሰው እንዳይላኩ ልዩ ጥበቃ ያሻቸዋል። በፍርሃትና በግዳጅ የተፈናቀሉ ስለሆነ በያሉበት ሰበዓዊ መብታቸው እንዲከበርና እንዲጠበቅላቸው መሆን አለበት። እንርዳቸው ከተባለም የተለመደው የፍራፍሬና የአትክልት ለቀማ ስራቸውን በመሃል ሀገሮች ውስጥ መልሰው የማግኘት እድል እንዲኖራቸው መንግሥቱ በመዋቅር ዝግጅቶችን ማቀነባበርም የሚሳነው አይመስለኝም... ………ጣሊያን ስደተኞችን በገፍ የመመለስ ፖሊሲዋን አሁንም እንደምታራምድ ብዙ ምስክር ማቅረብ አያስፈልግም። ይቀጥላል


20 / 01 / 10 አብራሃም ዘውዴ (ቦሎኛ)


Bianco natale


ይድረስ ለባቦ ናታሌ...!


Azeb Luca Trombetta / ከአዜብ ሉካ ትሮምቤታ 25 12 09


………Carissimo Babbo Natale… ………Così cominciano le lettere più famose nella storia del mondo. Ma oggi l’indirizzo è diverso non più “Santa Klaus, North Pole”; ma è più probabile ottenere risposta indirizzando la lettera a qualche centro di detenzione del posto. ………Sì, perché la notizia è di qualche giorno fa: negli USA si nasconde un pedofilo sotto la barba di qualche Babbo Natale. Ed ecco che uno dei miti d’oggi dei bambini si snatura nella trappola dell’indecenza. E già i primi dubbi, le prime riflessioni e la prima rabbia e la paura per il futuro, per i figli e per noi che vogliamo ancora essere bambini. Ma questo natale non è facile per nessuno: i bambini hanno perso un eroe, i grandi non hanno soldi per regali spesso inutili e, rullo di tamburi, il gioco di capodanno non è più la tombola, ma la caccia al clandestino. ………La notizia, sempre di questi giorni è: White Christmas. Caccia al clandestino in nome del natale. ………Succede in Italia, nella mia nazione che si dovrebbe basare sul terzo (senza contare gli altri) articolo della costituzione: “Tutti i cittadini hanno pari dignità sociale e sono eguali davanti alla legge, senza distinzione di sesso, di razza, di lingua, di religione, di opinioni politiche, di condizioni personali e sociali. È compito della Repubblica rimuovere gli ostacoli di ordine economico e sociale, che, limitando di fatto la libertà e l’eguaglianza dei cittadini, impediscono il pieno sviluppo della persona umana e l’effettiva partecipazione di tutti i lavoratori all’organizzazione politica, economica e sociale del Paese.” ………succede sotto il tetto natalizio, in quel breve periodo dell’anno in cui si dice ai bambini (sempre a loro che, poveretti, si sorbiscono la nostra ipocrisia) di essere più buoni. ………Succede, ma tutti siamo troppo impegnati ad impacchettare e spacchettare regali, a fare l’albero, a ricordarci di non fare nascere il Bambinello prima del tempo e a fare la lista del menù per i vari pranzi e pranzetti. ………Qualcuno però si è già armato di pala per ripulire le strade, le case, i bar dai quei strani soggetti che portano il nome di “clandestini”. Come ben sapete non voglio fare moralismi, soprattutto in un momento in cui il peso del pranzo prende vita in un abbiocco stratosferico, ma sull’onda del buonismo incessante di questi giorni voglio condividere con voi le mie riflessioni. ………Perchè nessuno si sta chiedendo come possa succede tutto questo? ………Perchè nessuno dei cattolici che passano la notte a pregare si ribella? ………Perchè? ………E poi, chi sono i clandestini? ………Mi rivolgo a voi più piccoli che avete ancora l’animo puro. Guardate i vostri compagni di giochi, i vostri compagni di banco, i vostri vicini di casa e dite a mamma e papà di non denunciare perchè quegli stessi bambini il prossimo natale potrebbero essere senza i genitori che sono stati arrestati oggi. I ragazzi che popolano le vostre scuole potrebbero essere figli di clandestini. Se vi hanno tolto i sogni riprendeteli aprendo gli occhi grandi e chiedete voi ai vostri genitori di essere più buoni almeno in questi giorni di natale

La tela bianca

Pubblicato da Azeb 4 12 2009

………I miei scritti, quelli che voi leggete (spero con piacere e curiosità) sono nati dentro un autobus, e solitamente continuano a prodursi nei miei (seppur brevi) viaggi. Il rapporto con questo mezzo di trasporto è quasi ancestrale: mi sento come dentro una pancia materna, dove riesco a sentire i suoni, la confusione, le musiche, ma soprattutto le emozioni. ………Solitamente mi siedo o sto in piedi nella zona centrale. Da lì passano tutti e la visuale è perfetta. Quando scrivo i pezzi cerco di ricordare le cose viste e cosa provo nel viverle. Ecco che un frammento diventa emozione e poi prende vita su un foglio. ………Cosa può succedere, mi sono chiesta, se ad un certo punto fossi costretta a stare in fondo all’autobus? Non per mia scelta, ma per un “tacito accordo” tra i passeggeri italiani e quelli stranieri? ………Faccio un passo indietro e vi racconto, così capite anche voi... ………Il 31 ottobre, sempre sul mio 27A leggo il giornale, la notizia è: “Sulla linea 81 tacito accordo: italiani davanti, stranieri dietro“. Il primo pensiero va indietro nel tempo, ma di questo ne parliamo dopo. Intanto il punto è: ma siamo certi che questo accada solo per la linea 81? Eh sì, ragazzi miei, il problema, o meglio, il “tacito accordo”, è più che diffuso nelle linee di Bologna. Se salite sull’autobus, qualsiasi linea, e osservate la disposizione cromatica all’interno, noterete come i colori scuri stiano in fondo e piano piano, in un perfetto gioco di sfumature, si arrivi al bianco caucasico tanto amato dall’aitante Hitler. ………Certo la storia artistica-sociale ha sempre avuto una certa passione per il bianco. Sapete, le tele nascono bianche, perché puoi coprirle di colore. E’ evidente a tutti che il fabbricatore di tele non possa essere ritenuto razzista, perché la tela bianca è il miglior supporto per un opera pefetta. Ma perché quell’opera diventa perfetta? Perché è una tela bianca coperta, in maniera armoniosa, di colore. Ecco cosa vorrei che la gente comprendesse. Non esiste un’opera d’arte fatta da una tela lasciata bianca, ma esiste un’opera d’arte che nasce su un supporto bianco e che si incrocia con le pennellate di colore.

Coliandro e gli stranieri

Pubblicato da Azeb 05 03 2010

………

………Il 28 febbraio CrossingTV ha incontrato Giampaolo Morelli, interprete dell’ispettore Coliandro, Carlo Lucarelli, inventore di Coliandro e tutti i loro fans, accorsi al Festival Visioni Italiane della Cineteca di Bologna per vedere in anteprima la puntata “666″ della serie televisiva non ancora andata in onda. ………Abbiamo focalizzato la nostra attenzione su uno dei temi affrontati dalla serie televisiva, che secondo noi è poco messo in risalto quando si parla del famoso ispettore, ovvero al rappresentazione degli stranieri. Anche Morelli, in arte Coliandro, è rimasto sorpreso dal tema dell’intervista: evidentemente nessun giornalista aveva toccato questo argomento con lui prima d’ora … intervista di Azeb Lucà Trombetta riprese e montaggio di Silvia Storelli ringraziamo Carlo Lucarelli, Giampaolo Morelli e la Cineteca di Bologna


ላቮሮ ሮማ...ወሰኔ አለሙ ከሰሜን አሜሪካ


………ጣሊያን አገር የደረስኩት ኦክቶበር 28 ቀን 1992 ነው። ከዛሬ አስራ አምስት አመት በፊት መሆኑ ነው። እኔ እዚያ ስደርስ ሮም ከተማ በገና በአል መብራት ደምቃለች። ማታ ማታ አለማቋረጥ ይዘፈናል። ድንገት ጦርነት አልቆ ከጦላይ ግዞት የወጣሁ በመሆኑ ግር አለኝ። እንዴት አይነት አለም ነው አልኩ። እውነት እላችኋለሁ ዞሮብኝ ነበር። ለአውሮፓ አዲስ አልነበርኩም። ባልኖርበት አልፌበታለሁ። ራሽያ ስሄድ በዚያው ነው ያለፍኩት። አየሩን አውቀዋለሁ። ሮማውያን ድደግግሞ ሁሉም ነገራቸው ፍቅር ነው። እንኳን ሴቶቹ ወንዶቹ ሲገናኙ ይሳሳማሉ። አሞሬ ሚዮ” ይባባሉ። የኔ ፍቅር፣ የኔ ወለላ፣ የኔ ማር፣ እንደማለት ነው ዝርዝር ትርጉሙ። “ኦስቲያ”ከተማ አንድ የስደተኞች ካምፕ ውስጥ ነበር የምኖረው። ካምፑ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ ስምንት ሰዓት ድረስ ዝግ በመሆኑ በጠዋት ተነስቼ መውጣት አለብኝ። እናም ወጥቼ ሮማ ከተማ እሄዳለሁ። ስምዖን መለስን ያገኘሁት እዚያው ሮም ነው። አባቱ አቶ መለሰ ፀጋየ በጣሊያን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሃላፊ ናቸው። ከስምዖን ጋራ እንደዚሁ ከምንዞር ብለን አንድ የነፃ የጥሊያን <አስኳላ> ትምህርት ቤት ገባን። እኔ እዚያ ቦታ የገባሁት እንደ ፓሮት የሰማሁትን እየደገመኩ ከማወራ ትንሽ በትምህርት የተገኘ እውቀት ጥሩ ነው ብየ ነው። “ወረቀት ያለ ይስቃል” ያሉትን አይነት ነው። እናም ሃሳቤ በትንሹ የሰራልኝ ይመስለኛል። ዛሬም ድረስ ትንሽ የጣሊያን አፍ አውቃለሁ። እንደም አደራችሁ! ደህና! ከማለት ያለፈ ማለት ነው። ብዙ አይደለም ግን ይገባኛል። የፈለገ ቢመጣ በጣሊያን አፍ አልታማም። ከስምዖን ጋራ ትምህርት እንደጨረስን ስራ ማፈላለግ ያዝን። ያኔ ጣሊያን ያለው ስራ ለሴቶቹ ብቻ ነው "ሲኞራ ቤት" ነው። እዚያ ነው የሚሰሩት። ነገሩ ያው ስሟ ላይ ነው እንጂ ብዙው እጅ ግርድና አለበት። ዋናው የስራ ምድቡ ማለት ነው። ጥበቃና ጉልበት አንድ ላይ ሆነው የሚፈጥሩት ድምር ነው። ጥጉ የሚባለው የሰራተኛና አሰሪ ኮድ ነው። በጣሊያን አፍ በመሆኑ ነው "ሲኞራ ቤት" የተባለው። ሴቶቹ እዚያ ይሰራሉ። ስምዖን ጋራ ስራ አፈላልገን ሲደክመን እቤቱ ይወስደኛል። አባቱ ጋሸ መለሰ ፀጋየ ጥሩ ሰው ነው ማለት የሚያንሰው ሰው ነው። ውብ ነው። ሸጋ ነው። ደግ ነው ተብሎ አንድ ቃል ወጥቶለት ጋሼ መለሰ እንደዚያ ነው ቢባል የሚገባው ሰው ነው። ጋሸ መለሰ በድሃ እናቱ እና በድሃ አገሩ የሚኮራ ትልቅ ኢትዮጵያዊ ሰው ነው። አንዳችንን ካንዳችን የሚያበላልጠን የኢትዮጵያዊነት መለኪያ ቢፈጠር ጋሼ መለሰ እጥፍ ያስከነዳናል። ከልቡ አገሩን ይወዳል። እንደዚያ አይነት ልብ ለሁላችንም ቢሰጠን የዘወትር ምኞቴ ነው። ይሄ ሆዳም ሆዳሙ ከጋሼ መለሰ ቢማር እላለሁ። አንድ ሰሞን ከስምዖን ጋራ ስራ ፍለጋ ልባችን ጥፍት አለ። ጠዋት ወጥተን ስራ መፈለግ ነው። በመሃሉ አንዲት ስምኦን የሚያውቃት ልጅ ስራ አለ አለች። ገና የስራው ምንነት ሳናውቀው ስምኦን ለኔ ስራውን ለቀቀልኝ። ትንሽ በእድሜ ሳልበልጠው አልቀርም። ማከበሩ ነው እግዜአብሄር ያክብረው። እናም እኔ አንድ ሰኞ በጠዋት ስራውን ለማየት ሄድኩ። ሮማ ከተማ ነው። ”ኖሜንታና” መንገድ ላይ ያለ አንድ የሃብታሞች ሰፈር ነው ስራው የተገኘልኝ። እዚያ ስደርስ ምን አይነት ስራ ሊያጋጥመኝ እንደሚችል እያሰላሰልኩ ነበር። ስራ ከተገኘልኝ ቤት ትንሽ ከፍ ብሎ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አለ። ባንዲራችን ከፎቁ ሁሉ በላይ ሆኖ ይውለበለባል። ባንዲራ ሳይ አንድ ሰውነቴን ውርር የሚያደርገው ነገር አለ። ስሜታዊ ያደርገኛል። ምናልባት እሱኑ ባንዲራውን ይዤ አገሬ ብከዳሽ ሞት እጣ ፈንታየ ይሁን ብየ ስለማልኩ ይመስለኛል እንደ “ፎቢያ” ወይንም “ፓራኖያ” አልያም የወንጀለኛለነቱ ስሜት እየተከተለኝ ይሆናል እኔ አላውቅም። ግን ሰውነቴን ይወረኛል። የቀጠረችኝ ልጅ መንገድ ላይ ወጥታ ተቀበለችኝ። ኤልሳ አለችና ስሟን አስተዋወቀችኝ። የኔን ተናገርኩ እና አብረን መንገዳችንን ቀጠልን። ሁሉም ቦታ አንድ አይነት ሆነው በተሰሩት ጠባቦቹ የጣሊያን መንገዶች እኔና ኤልሳ ተያይዘን ስንሄድ <ለመሆኑ ምን አይነት ስራ ነው> ብዬ ልጠይቃት እያልኩ ሳስብ ድንገት አንድ ትልቅ በር ላይ ደርሳ <ይሄ ነው ቤቱ አለች እና አሳየችኝ> እንደማንኛውም የጣሊያን ቤት ሳይሆን አንድ ቦታ ላይ ትልቅ ሆኖ የተሰራ በረንዳው በነጭ እብረ በረድ ልቅም አድርጎ የተሰራ የምድር ገነት የሚመስል ቤት ነው። ኤልሳ እዚህ ነው አለችና ግድግዳው ላይ ያለ አንድ ነጭ የቤት ደውል ተጫነች። ኪ ኤ! የሚል ቀጭን የጣሊያን አሮጊቶች ድምፅ ሰማሁ። ማነው? መሆኑ ነው። ኢዮ ሶኖ ኤልሳ አለች። ኤልሳ ነኝ ማለቷ ነበር። ያ የመንግስተ ስማያት መግቢያ የመሰለ ትልቅ በር ተከፈተ። ጊቢው ባማረ አበባ አጊጧል። አንድ እንደኔው ጥቁር ሰው የአበባ መኮትኮቻ ይዞ መሃል ጊቢው ውስጥ ቆሟል። የምእራብ አፍሪካ ሰው ይመስላል ነገሩ ይሄኔ አንቱ የተባለ ሰው ነው እያልኩ በጭንቅላቴ ብቻ ሰላም አልኩት። “ቻዎ አሚጎ” አለና እስከ መሃል ሮማ ድረስ እንዲሰማ አድርጎ ጮሆ ሰላም አለኝ። ቤቱ ውስጥ ሲገቡ ደረጃ ያለው ነው ወደ ላይ የመኝታ ቤት ሲሆን ምድር ቤቱ እርስ በርሱ በተያያዘ ሳሎን እና የምግብ ቤት አለው። መልኩ ቡናማ የሆን ሰፊ የቆዳ ሶፋ ወንበር ቤቱን ሞልቶታል። አንድ ጥግ ላይ ትልቅ የግድግዳ ሰአት ተሰቅሏል። ቀና ብየ አየሁት አምስት ሰአት ይላል። ከሰአቱ ስር የአንድ ትልቅ የቤተሰብ ፎቶ አለ። የልጅ ልጅ ሁሉ ያለበት ይመስላል። የቤቱ ንፃት ሰው ያለበትም አይመስልም። እንደዚህ እያልኩ ግራ ቀኙን ሳይ አንድ በአካለ ስንኩላን ጋሪ የሚሄድ ሰው ከአንድ ጥግ በኩል ብቅ ብሎ <ቻዎ > ኤልሳ ሲላት እና የቤቱ ዋና መብራት ድንገት ሲበራ አንድ ሆነ። ይሄ ነው ከጃስፐር ጋራ ሊሰራ የመጣው አላት። አዎ ሲኞሬ ጆቫኒ አለች እና ኤልሳ መለሰች። ኮሜቲ ኪያሜ! አለኝ “ወሰኔ” አልኩ። ዶቬ ሴይ? ኢትዮጵያ ከማለቴ... ስማ ከዚህ በፊት ምን ትሰራ እንደነበር ማወቅ አልፈልግም። ምናልባት የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንትም ትሆን ይሆናል እያለ ፈገግ አለና። እኔ አሁን የምፈልገው እንደምታየው ያለሁት በዚህ ጋሪ ላይ በመሆኑ ውሻየን ጃስፐርን በየጊዜው እያወጣህ እንድታንሸራሽረው ነው። ይሄን ማድረግ ትችላለህ አለኝ ሲኞር ጆቫኒ። የምን ውሻ ነውየሚያወራው? እያልኩ ዘወር ብየ ወደ ኤልሳ ከማየቴ አንዲት በአስራ አመቶች ውስጥ የምትገኝ ልጅ እዚያው ሳሎን ውስጥ ካለ አንድ ክፍል አንድ ፀግራም ውሻ ይዛ ብቅ አለች። የወጣችበት ክፍል ሲከፈት ቤቱን <የቦኒ ኤም > አንድ ክፍል የሆነው <ዳዲ ኩል > የሚለው ሙዚቃ ሞላው። ክፍሏ ሆና የምታዳምጠው ሙዚቃ ነበር። ይሄን ዘፈን አንዴ ሌኒን ግራድ ከተማ በቀጥታ አንድ ትልቅ ኮንሰርት ላይ በቀጥታ ሲተላለፍ አይቼዋለሁ። ዘፈኑን ያየሁት ወንድሜ ጋብዞኝ ከኪርጊዝ ሪፐብሊክ ተነስቼ ሄጄ ነው። ያኔ ይሄን ዘፈን ሳየው ለአገሬ እንደ አምባሳደር ሆኘ ነው ተማሪ ነበርኩ። አገሬ የላከችኝ በተማረው ትምህርት አገሩን ያገለግላል ብላ ነበር ይሄ ከሆነ በዚያን ጊዜ አስር አመት አካባቢ ቢሆነውም አሁን ግን ለአንድ ውሻ ዘበኝነት ተቀጥሬ ለዚያ ግልጋሎት ለመስጠት አንድ የፈረንጅ ሳሎን ውስጥ ነኝ ያለሁት። በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ life is not fair አልኩ። እንዴት እንደዚህ ሊሆን ይችላል እዚህ ቦታ እንዴት ልደርስ ቻልኩ? እያልኩ ሳስብ ድንገት የአንቶኖቭ አውሮፕላን ድምጽ ትርርርርርርርርርርር… ደግሞም እኛ የደብረ ዘይቶቹ <ኡዴ> ከምንለው አካባቢ የተዋጊ ጀቶች ድምፅ ካኪ ሱሪ ቦንበር ጃኬት ያደረጉ ቀጫጭን ረጃጅም ሰዎች ጠይሞቹ ደብረ ዘይት መንገድ ላይ ”መቶ አለቃ” እንደምን ዋልክ... የሚል ድምጽ ሁሉም አንድ ላይ በፊቴ አለፈ። ይሄ ነው ሰውየው? አለችና ልጅቷ ስትጠይቅ ድንገት ነቃሁ ። <አዎ የኔ ጣፋጭ > አላት። ሲኞር ጆቫኒ ። በዚህ መሃል “ጃስፐር” የተባችው ውሻ እግሬ ስር ገብታ ትልሰኝ ጀመር ። ወሰኔ! ውሻዋ ይቺ ናት ከሰዓት እየመጣህ እዚህ ታች ያለው መናፈሻ አንድ ሁለት ሰአት እንድታንሸራሽራት ነው። ስራው ቀላል ነው። እያለች በማዘን እና በመገረም ታየኝ ጀመር። አስተያየቷ አየ ወላድ! እናቱ ይሄን አላየች የሚል ይመስላል። ለመሆኑ ክፍያው እንዴት ነው አልኩ ፡ይሄን ስል ፤ውሻዋን ለመጠበቅ ተስማምቼ፤ዋናው ፍራንካው ላይ ነው ለማለት ነው። ኩዋንቶ ሶልዲ ፤ባጋሬ፤ ፐር ሉይ ?አለችው ። ሲኞር ጆቫኒ… እንደሌሎች ዘመዶቹ ሁሉ አፉን እጁ ላይ አድርጎ… ኤ...ኤ...እያለ። <ዱዌ ቼንቶ ፐር ሴቲማና > ባቤኔ! አላት። ሁለት መቶ ሺ ሊሬ በሳምንት ማለቱ ነው። የጃስፐር የጥበቃ ሃላፊ ሆኘ አውሮፓ ውስጥ ስራ የጀመርኩት በዚህ አይነት ነበር። ስራየን የምጀምረው ሲኞር ጆቫኒ የከሰአት እንቅልፋቸውን ሲወስዱ ከቀኑ ስምንት ሰአት ጀምሮ እስከ አስራ አንድ ሰአት ሲሆን ያን ጊዜ ጃስፐርን ይዠ ወደ መናፈሻው እሄዳለሁ። የስራው ዝርዝር ።  8፤ 00 ሰአት ጃስፐርን እረከባለሁ። ጃስፐር ስታየኝ ነፍሷ እስኪጠፋ ትዘላለች ስትወደኝ አለሙ ሁሉ አይበቃትም ኋላ ላይ ኤልሳ አየህ የነፍስ ነገር ልክ አንተ በምትመጣበት ሰአት በር በሩን ማየት ትጀምራለች ብላኛለች።  8፤ 15 እኔና ጃስፐር ፤ፓርክ እንደርሳለን።  8፤ 30 የፓርኩ ዘበኛ ጃስፐር ድንገት የተፀዳዳች እንደሆነ፤ጉዳይዋን የማፀዳዳበት ላስቲክ ይዥ እንደሆን ይቆጣጠራል።  8፤ 35 ጃስፐርን ለቅቄ አዝናናታለሁ ።  8፤ 40 የጃስፐር አይነት የመንዱሩ ውሾች ይመጣሉ ።  ከቀኑ 9፤ 00 ጠቅላላ የውሻ ጠባቂዎች ይሰበሰባሉ፤ እናም፤ የቪኖ መጠጣት ስነስራት ይጀመራል፤አዲስ ቪኖ ከተማው ውስጥ መጥቶ እንደሆን ከአባላቱ ይቀርባል።እዚህ ስብሰባ ላይ አንዳንዴ ስደተኛ ሴቶች ሁሉ ይመጣሉ ፤እነሱም እንደኛው ውሻ የሚጠብቁ ናቸው።  10፤ 45 ሁሉም ውሻ ጠባቂ ፤ውሻውን ይጠራል ።እና ወደ ቤት መንገድ ይጀመራል ።  11፤ 00… . ጃስፕር ወደ ቤት ትገባለች።

ስራውን ከጀመርኩ ከሁለት ወር በኋላ።

ቸኩያለሁ ፤ተርሚኒ የሮማ ዋና መሃል አራዳው ነው እምብርቱ ነው እንደሚባለው ነው። ለስደተኞቹ እንደ ነፃ መሬት ያገለግላል። እዚያ የጣሊያን ፖሊስ ጉልበት የለውም። ህገ ወጥ የሆኑ ስራዎች በሙሉ የሚሰሩት እዚያ ነው። እንደዛሬ ነገሮች ሳይካረሩ በፊት ድንገት ጠዋት ተነስተው ከቤት ወጥተው ማታ ላይ የፈለጉትን አይነት አገር ዜግነት አግኝተው ፓስፓርት ከልደት ሰርቴፊኬት ጋራ ይዘው የሚመለሱበት ቦታ ነው። አራት በአራት ጉርድ ፎቶ እዚያው ተነስተው ”አብደላዚዝ አብዱል መንሱር” ተብለው የሱማሊያ ተወላጅ መሆን የሚቻልበት ቦታ ነው። ተርሚኒ እንደዛ ነው። ስልክ አዲስ አበባ ለመደወል ከፈለጉ አንድ ሰው መንግስት ያቆመውን የመንገድ ላይ ስልክ በምን ጥበብ እንደሆነ ሳያውቁት መጠነኛ ገንዘብ አስከፍሎ ለማንኛውም ኢንተርናሽናል ጥሪ ከፍቶሎት የሚሄደው ተርሚኒ ነው።እናም ድንገት የጣሊያን <ፔሮኒ > ቢራ ወሳስደን ሞቅ ያለን ለት “ተርሚኒ ነው ቤቱ ያበራል ጥይቱ” ብለን እናንጎራጉራለን። ይሄ የተለየ አርብ ቀን ተርሚኒ ከጓደኞቼ ጋራ ጥብቅ ቀጠሮ በያዝኩበት ሰአት ሲኞር ጆቫኒ እኔን ሳያይ እንዳይሄድ ብለውሃል አለችና ኤልሳ ነገረችኝ። ለምን ?አልኩ ኮስተር ብየ። እኔ አላውቅም ! ብቻ ሲመጣ እፈልገዋለሁ ብለዋል አለች። ከቀኑ አስራ አንድ ሰአት ላይ ሲኞር ጆቫኒ ፤ከሴት የልጅ ልጃቸው ጋራ መጡ፤ እና ሳሎን ተቀመጡ። ጃስፐር አንድ ትልቅ ቅርጫት ውስጥ ሆና ሙሽራ መስላ መጣች። ሳያት ከቅርጫቱ ወጥቼ ካልተጠመጠምኩበት ብላ አስቸገረች። “ስታ ዚቶ” ጃስፐር አሉና ሲኞር ጆቫኒ ጮሁ ለጣሊያን መጮህ አዲስ ባይሆንም የዚያን ቀን ጩሀታቸው ግን እንደ ማስደንገጫ ነበር። ውሻዋን ዝም በይ ለማለት ነው ጩሀታቸው። እኔ አደባባይ ከሚያክለው ሳሎን ውስጥ ቆሜያለሁ። ስማ! ውሻዋን ስትጠብቅ እንዴት ነው? ብቻዋን ጥለሃት ሄደህ ታውቃለህ? ከሌሎች ውሾች ጋራ አንድ ላይ ትሆናለች? አሉና ጠየቁኝ። እኔ የትም ጥያት አልሄድም ከሌሎች ውሾች ጋራም አትሆንም አልኩ። እና ማን ነው ያስረገዛት? አንተ ነህ ያስረገዝካት? ዛሬ <አስፔዳሌ > ወስጃት ሃኪሙ እርጉዝ ናት ብሏል እና ለዚህ ምን መልስ አለህ አሉና ትኩር ብለው ያዩኝ ጀመር። እንደዚያ ትኩር ብለው ሲያዩኝ የሰው ነገር እሱ ይሆን ይሄን ያደረገው ብለው ነው። ስደት ላይ አንዳንዴ የባህል ግጭት አለ አንዴ አንድ የ <ጋና > ሰው እሱ የተወለደበት አካባቢ የዝንጀሮ የውስጥ አንጎል እኔ ነኝ ላለ እንግዳ የሚቀርብ ትልቅ ምግብ እንደሆነ ነግሮኛል። አንድ የቻይና ዘር አለ። ልጃቸውን ከመዳራቸው በፊት ለሚመጡት ሽማግሎች የሚቀርበው ምግብ መንደር ውስጥ ቦቢ እየተባለ ያደገ ውሻ ነው። ድንገት ይሄ ሳይሆን ሲቀር ሽማግሎቹ ምን እሱ በሬ አርዶ ነው የተቀበለን ንቆናል ብለው ያማሉ። ሲባል ሰምቻለሁ እናም በሲኞር ጆቫኒ አልፈረድኩም ይሄን አድርጓል ብለው ቢጠረጥሩ አያውቁኝም ለማንኛውም። እኔ እንዴት እንዳረገዘች አላውቅም አልኩ። ይሄን ማለቴ ራሴን ነፃ ለማውጣት እንጂ እዚያ መናፈሻ ቦታ እኔ ቪኖየን ስቀመቅም አንዱ የመንደር ጎረምሳ ውሻ ጉድ እንደሰራኝ አውቄያለሁ። ጃስፐር ቅርጫቷ ውስጥ ሆና ወደ እኔ ታያለች። ማን ምን እንዳደረጋት እሷ ታውቃለች፡ ከዚያ ሁሉ መንጋ ውሻ ስራውን ማን እንደሰራ የምታውቀው ጃስፐር ብቻ ናት። እናም ስታረግዝ የውሻ ውበቷ የወጣ መስሎ ታየኝ። እና! አሉኝ ሲኞር ጆቫኒ። እና! አልኩ እኔም መልሼ እና! በጣሊያንኛ ሲሆን < አሎራ > ነው የሚሆነው። አሎራ! አልኩ እኔም ሁለት መቶ ሺ ሊሬ በጃቸው ይዘዋል። የመጨረሻው ክፍያ መሆኑ ነው። ከዚህ በኋላ እዚህ ቤት ከኔ ጋራ ልትሰራ አትችልም አሉና ነገሩኝ። የመጨረሻ ደሞዜን ተቀብየ ከሲኞር ጆቫኒ ቤት ወጥቼ ስሄድ መሽቷል ለገና በአል በየቦታው የተተከለው መብራት ብልጭ ድርግም ይላል አዲስ አመት ቅርብ ነው ዘመኑ 1992ነበር። ዛሬ እንኳን የፈረንጆቹ የኛም ሚሌኒየም ሊከበር ነው በዚያ ዘመን ግን እንደዚህ አይነት ታሪኮችም ነበሩ። ይሄን ለሚያዩ ሁሉ እንኳን ለአዲስ አመት እላለሁ፤ እንኳን ለሚሌኒየም አደረሳችሁ። ደግሞም በሶስት ሺ ለመገናኘት ያብቃን። እመኑኝ ሁላችሁንም እወዳችኋለሁ። እንደገና በሌላው ዘመን የምትፈጠሩ ከሆን ስደተኛ አትሁኑ፡ ኢትዮጵያ አገራችን ለዘላለም ትኑር ።



እዚህ ጣሊያን ሀገር የሰለቸኝ...

* ልብስ ማጠብ ወይንም ላቫትሪቼ ማድረግ፣ ደግሞ እንዲደርቅ ፀሀይ ላይ ማስጣት፣ መተኮስ፣ ...
* ምግብ መስራትና ከዚያ የበላሁበትና የሠራሁበትን ሳህና ድስት እቃ ማጠብ ነው የሰለቸኝ። ይህንንም ፓርት ታይም ስራ ብዬዋለሁ። ወይም ሁለተኛ ስራ ሆኖብኛል። ምንም የእውነት እረፍት ቀን የለም እኮ!! ያችኑ እሁድ ቀንን እንዲሁ ስል ምንም ሳልቀመጥ ቀኗ ታልቃለች። ሀገር ቤት ላሉ ለቤት ሰራተኞች እጅግ አዘንኩላቸው። ያ ግፍ ይሆን እንዲህ እንድሆን ያደረገኝ? እናት አባቴ በሰፈሩበት መስፈሪያ እኔው እየከፈልኩት ነው። የሰራተኞቹ ጡር ነው መሰለኝ የደረሰብኝ።
* አንዳንዴ የእንጀራ በወጥ አምሮቴን ለመወጣት ብዬ ያው በመጥበሻ (padella) ላይ እንጀራ መጋገር፣ ቆንጆ ወጥ ለመሥራት አይኔ እስኪቃጠል ድረስ ሽንኩርት ስከትፍና ሳቁላላ መዋል ... ከዚህም አልፎ ተርፎ ወደውጪ ስወጣ ወጥ ወጥ እየሸተትኩ መውጣቱ። ይህ ችግር በኔው አፓርትመንቶ ውስጥም አለ። ክፋቱ ደግሞ ልብሱ አንዴ ከሸተተ ወድያው ላውንደሪ ካልተወረወረ አርማዲዮ ውስጥ ያለውን ሁሉ ይበክለዋል። እኔ የምለው - በዚህ ጉዳይ ምን ቢደረግ ይሻላል ትላላችሁ? አገር ቤት እያለሁ እንዲህ አይነት ችግር አልነበረም እኮ! ወይም አይታወቀንም ነበር መሰለኝ? ምክንያቱ ማድቤታችን ለብቻ ራቅ ያለ ስለነበር ነው እንዳልል የብዙዎቻችን ቤት መኝታ ቤቱም ሳሎኑም ኪችኑም አንድ ላይ ነው። ለዛውም በከሰል ወይም በናፍጣ በሚሰራ ምድጃ እየተጠቀምን...
* በጣሊያን ሀገር ከደባል ጋ መኖር የተለመደ ነው። በተለይ የምንከራየው አንድ አፓርታመንቶ ከሆነ አንዱን ክፍል ይዞ መኖር የተለመደ ነው። መቼም በአብሮ መኖር ላይ ስንት አይነት ፀባይ አለ መሰላችሁ። ብቻ ትግስት የሌለን ከሆነ…

* ሌላው ደግሞ ሱፐር ማርኬት መመላለሱ። መቼም እኔ እንደሱ የሚያስጠላኝ ነገር የለም። አንዳንዴማ በየጊዜው እየሄዱ አስቤዛ ከማድረግ ብዬ እንደው ምንም ሳልበላ ጾሜን የማድርበት ጊዜ አለ። ማን ምግብ ይቀቅላል። ተመልሼ አዲስ አበባ ሂጂ በሰራተኛ ለመኖር ጊዚው ነው የናፈቀኝ። ግን እኒ እንደ ቢተሰቦቼ አልሆንም። ችግራቸው በደንብ ስለግባኝ ሰራተኞቼን በደንብ እይዛቸዋለሁ።...
* ሌላው ስልቺት ያለኝ ወደ ሥራ ለመሄድ ጠዋት ጠዋት የእንቅልፍ መቀስቀሻው ሰዓት (la sveglia)። ጥዋት በ6 ሰዓት ላይ Kirrrrrrr እያለ የሚጮህው። በተለይ አምሽቼ ስተኛ ጥዋት ላይ ደስ የሚል ህልም እና እንቅልፍ ላይ እያለሁ ! እኔ እንደው ገሀነም ሲገባ እሳት ብቻ ሳይሆን የዚህች የተረገመች ሰዓት አላርም ሁሉ የሚንጫጫ ነው እሚመስለኝ። ... ይቀጥላል ...
* ሌላው ደግሞ የስለቸኝ እዚህ ያለውን የአበሻውን የተከፋ ፊት ማየት። ሳቅና ጨዋታ ያለበት ወይም መዝናኛ ያለበት ቦታ አለመኖሩ መሰለኝ!! በዚህም ምክንያት ይመስላል ሁል ጊዜ አበሻው የተከፋ ፊት ያለው ነው የሚመስለው። (በእረፍት ጊዜያችን እንኳ ይህ ነው የሚባል ዝግጅት ተባብረን ማድረግ ስለማንችል ይመስለኛል። አንዳንዶቹ አስተባብረው ለማድረግ ሲጥሩ ቋሚ ሕብረት ያጣሉ።
* ዋናውን እረስቼው!!! የዚህ ሀገር የአየር ፀባይ!!! ብርዱ ያው ብርድ ሲሆን፣ ሙቀቱ ደግሞ እሣት በመሆኑ። እኔ ያደግኩት umidita የሚባል ነገር የሌለበት ያማረ ጸሀይ ያለሀሳብ እየጠጣሁ ተፈጥሮ ያደላት ውብ አገር ውስጥ ነበር:: ታዲያ የዚህ አገር የአየሩ ሁኔታ 9 ወር ሙሉ ጥቅጥቅ ያለ ክረምት ነው። ክረምት ቢሉ ደሞ እንደኛ አገር በቆሎ እሽት በከስል እየተጠበስ መንገድ ላይ የሚሽጥበት እና ዝናቡ አንድ ጊዜ ብቻ ዘንቦ ወዲያው ጸሀይዋ ፈገግ ብላ በደስታ የምትወጣበት አይነታይደለም እኮ!!
እዚህ እኮ ግርም የሚለኝ አንዳንዴ ከጠዋቱ በ 8.00 ሰዓት ስነሳ ከምሽቱ በ 8.00 ሰአት የተነሳሁ የሚመስለኝ። ይታያችሁ እስቲ! ጠዋት በ8፡00 ሰዓት ገና ጨለማ የሚሆንበት አገር! ደግሞ በረዶ የጣለ ጊዜ ስትራመድ ጉልበት ላይ የሚደርስ ወይም ቅዝቃዜው አጥንት የሚስብር አይነት ክረምት ነው።
እንደምንም አይኔን ጠራርጌ ተነስቼ የምስራውን ስራርቼ ሳልጨርስ alle 4.00 di pomeriggio ድቅድቅ ያለው ጨለማ ይመጣል። ምን እሱ ብቻ ያንን ብርድ ለመከላከል ግማሽ ቁምሳጥኔን የያዘውን የክረምታቸውን ጃኬትና ለብርዱ ደግሞ ከሱሬዬ በታች ሌላ ቱታ ለብሼ ነው የምውለው።
ደግሞ እፎይ ጸሀይ ወጣልን ከመባሉ ከፈረንጆቹ ጋር buongiorno ስትባባል ወዲያው ስለአየሩ ቁንጅና ወሬ ይነሳል። እነሱም ያው በማጋነን ሲያወሩ ሁልጊዜ መስማቱ ስልችት ብሎኛል። ግን አይፈረድባቸውም። እራሳቸውም እዚሁ ተወልደው እዚሁ አድገውበት አለመዱትም መሰለኝ። ታዲያ እነሱ እዚሁ ያልለመዱትን እኛ እንዴት አድርገን?
ጉድ እኮ ነው ደሞ ይሄም ሙቀት ውበት ሆኖ!! እንዴ! ታዲያ ወበቁ አያስቆም፣ አያስቀም፣ አያስተኛ፣ በእዛ ላይ ቤቶቹ ከማርጀታችው የተነሳ ... ልክ በባዶ ድስት ወይም በእንፋሎት እንደተቀቀለ broccoli ሆኖ መዋል ነው።
አይ አለመታደል በዚያ ላይ የሚውዱት የበጋው ወቅታቸው ስትመጣ ቀኑ አጥሮ ቁጭ። ማታ ከስራ ደክሞኝ መጥቼ ዛሬ በጊዜ ለጥ ነው እላለሁ ብል ጸሀይዋ አትጠልቅ። እስከ ምሽቱ 9.00 ሰዓት ድረስ አይኔን እያጠናገረች። ያው ወደ 10.00 ሰዓት ላይ እንደው ገርበብ ሲል አይ የራሱ ጉዳይ ብዬ አይኔን እንደጨፈንኩኝ ከመቼው እንደሚነጋ አትጠይቁኝ። እንደምንም አይኔን እያሻሽሁ ስዓቱን ስመለከት ገና ከንጋቱ 4.00 ሰዓት ነው። ይሄ ታዲያ ኑሮ ነው ???
.
* እነዚህ ነጮች እንደው አንዳንዴ ጭንቅላታቸው እንደ ቂጣቸው ሊጥ ነው ልበል? አፍሪካ ሲባሉ ካለ ዝሆንና አንበሳ በቀር የት እንዳለች እንኳን ጨርሰው አያውቁም:: በተለይ ወጣቶቹ ከኢትዮጵያ ነኝ ስትላቸው የት ናት ይሉሀል። አፍሪካ ውስጥ ስትል አፍሪካ ያለችው ላቲን ውስጥ ነው? ብለው ሲጠይቁህ አንጀትህን ነው የሚቆርጡት:: እንደውም አዛውንቶቹ ይሻላሉ። በተለይ በሀይለስላሴ ወይም በአድዋ ጦርነት እንዲሁም ቅኝ ባለመያዛችን ለይተው ያውቁናል::
* አንዱ በጣም በዌስተርኑ አለም ከሚያስጠላው ነገር የራስን የቅርብ ጎደኛ ለሌላ ሰው ማማት፣ ሚስት ባልን ማማት ባል ሚስትን ማማት፣ በጣም አስጸያፊ ነገር ወሬና ወንድም እና እህት እንደትልቅ ጠላት መተያየት በትንሽ በትልቁ፣
* ሌላው ደግሞ በጣም ከሰለቸኝ ስም ሀበሻው ሁሉ በሌለው ስም መጠራት
* የአበሻ እድሜ ቀረጣ። ውጪ ከሚገኘው አበሻ መሀከል ብዙዎቹ እድሜያቸውን ቆርጠው ነው የሚናገሩት። አንዳንዴማ ፈረንጅ ፊት እድመያቸውን ሲገመድሉት ያስደነግጡኛል።
* ካልሳቅህ የፈረድብሃል የተባለ ይመስል ከድድ እስከ ድድ የሚስቅ አስመሳይ
* በየቀኑ በዜና ላይ እከሌ ሞተ፣ የከሌ ቤት ተቃጠለ፣ እከሌ ጠፋች ... አንድም ጥሩ ዜና የለም እኮ!!
* እዚህ ተዘፍዝፎ አገርቤት ያሉት ምን ማድረግ እንዳለባቸው መለፍለፍ ...
* በጠባብ ካሜራ ወይም በትንሽ አፓርታመንቶ ውስጥ ከሌላ ሰው ጋር ተከራይቶ መቀመጥ። ... ... ...
* እኔን በጣም ከሚገርሙኝ ነገር ደግሞ የአፓርታሜንቶ ጎረቤትን ያለማናገር አንዱ ነው። መፈራራት ነው መሰለኝ። ግፋ ቢል buongiorno ወይም buonasera ነው እንጂ ምንም ስለነሱ አታውቅም። እነሱም ስለአንተ አያውቁም። ለምን እንደሆነ አይገባኝም። ... ይቀጥላል ...
* ሌላው እዚህ አገር ስልችትና ድክም የሚያደርገኝ የቴሌ ማርኬቶች የስልክ ጥሪ FastWeb, Alice, Tele2 ... ወዘተ ... በተለይ ስልኩን ቶሎ ላለመዝጋት ብዬ ላዳምጣቸው ከአልኳቸውማ! በጥያቄ ራሴን ያዞሩኛል። ስልኩን እንኳን መዝጋት አልችልም። እስኪ ይህንን ምን ትሉታላችሁ?
* ሌላው "እዚህ ከመጣህ ስንት ጊዜህ ነው?" የሚለውና "ከየት ሀገር መጣህ?" የሚለው ደረቅ ጥያቄ ... ይቀጥላል ...
ሌላውን የሚሰለቸኝን ነገር በሌላ ጊዜ። እናንተም ጨማምሩበት ታዲያ! ........
እስከዛው ይመቻችሁ
ሚካኤል ስልቹው እስቲ በተቃራኒው እናንተ ደግሞ እዚህ ሀገር ደስ ከሚላችሁ ነገር በሚል አርዕስት ጫር ጫር አድርጉ ...

እዚህ ጣሊያን ሀገር ደስ ከሚለኝ

እስቲ መቼም እዚህ የሚሰለቸንን ያክል ደስ የሚል ነግርም ስለሞላ አንድ እንበል። እናንተም የምትወዱትንና በጣም የሚጥማችሁን ነገሮች እስቲ ጠቁሙ::
እኔ በበኩሌ በጣም ደስ ከሚለኝ ነገር ምግባቸው በተለይ ጣት የሚያስቆረጥመው ፓስታ አል ፎርኖ። ነፍሴ ነው።
ከሀገራቸው የወቅት ግዜያቸው estateውን በጣም ነው የምወድላቸው። ምክንያቱም የሚያማምሩ ሴቶች ጥብቆና ሚኒ አድርገው በተለይ ደግሞ ወደባህር ያለበት ሀገር ሄደህ በገፍ በኮስቱሜ እየሆኑ ወዲህ ወዲያ ሲሯሯጡና ሳያቸው ከክፍያ ነጻ መመልከትን የመሰለ ነገር የለም። ስትሪፕ ክለብ በአደባባይ ማለት እኮ ነው። እንደው ሲመቹ!
ሌላው ደግሞ ትንሽ ሊያስቃቹህ ይችላል ግን እዚህ ሀብታም ነኝ ድሀ ነኝ የሚል ልዩነት ሳይኖር ሁሉም በአንድ ማርኬት ውስጥ ባንድ ላይ የፈለኩትን ነገሮች ጋዛዝቼና (ያው ሀብታሙ የሚበላውን ምግብ ሁሉ ገዝቼ) እኔም መብላቴ። ታዲያ ይህ ይህ ነገሮች ሀገር ቤት እንደህልም ናቸው።

የነጮች አክብሮት ኢንፎርማሲዮኔ ወይም መንገድ አሳዩኝ ብለህ ስትጠይቃቸው ባያውቁኝም መልሳቸውና ሰላምታቸው እንዴት አደንቀዋለሁ መሰላችሁ። በሁሉም ቦታ ለሁሉም ነገር grazie የምትለው ትህትናቸው። የሌላውን አላውቅም እንጂ ይሄን ሀገር በሰውነቴ ተከብሬ ስለምኖርበት እውደዋለሁ

በግሌ ደግሞ ደስ የሚለኝ የራሴን ኑሮ መኖር መጀመሬ አገር ቤት ብሆን ኖሮ ይኼኔ ሥራ ሁላ ብሰራ ከአባቴ ቤት አልወጣም ነበር ሁልግዜ ልጅ እንደሆንኩ የምኖር የመስለኛል::

እኔ ደስ ከሚሉኝ ነገሮች ውስጥ የትም ውዬ ድክም ራብ ብሎኝ ስገባ እድሜ ለ congelati በትንሽ ደቂቃዎች micronde ክትቼው አብስዬ ስበላ .....አይ እናቴ ጉዴን አላየሽ ሽንኩርት መላጥ የለ መክተፍ የለ .......ግልግል እላለሁ:: ብቻ ሁል ጊዜ እሱን ስበላ ራሴው ላይ ምግቡ እንዳይበቅልብኝ ፈርቻለሁ።
አሁንም ሆዳም እንዳትሉኝ ስው እቤትህ ቢመጣና ምንም የሚበላ ነገር ከሌለ እድሜ ለ pizza d'asporto ወይም ለቻይና ምግብ። እዛው ቤትህ ቁጭ ብለህ ከዲቫኖ ሳትነሳ በስልክ ማዘዝና እንግዶችህን ማስተናገድ። ኤውሮህን ይጭነቀው እንጂ።
እዚህ ደግሞ ከፈረንጆቹም ጋር አብረህ ስትውል ጋብዘኝ ልጋብዝህ አንተ ክፈል እኔ ልክፈል የለ። የየራስህን ከፍለህ ሳትጨናነቅ በጋራ መዝናናት እያለ። ስለአንተ ማንም አያገባውም የፈለከውን ታረጋልህ :: ይሄ ከምንም በላይ የምወደው ነው :: ምን ያህል ዲሞክራሲና ነጻነት እንዳላቸው ያው እንደምታውቁት ነው እስከ አፍ ጢምህ ድረስ ነው ያለህ። ሀገር ቤት እያለሁ ገበያ አልችልም ነበር:: ገበያ ከሄድኩ ስለማልከራከር ከስሬ እመጣለሁ :: እዚህ ግን ቀንስ፣ መሸጫውን፣ መርቅ ... የለ። ዋጋውን እንቅጩን አውቀህ ወይ ትገዛለህ ወይ ትሄዳለህ። 4. የፈለከው ቦታ መብላት - ሆዳም እንዳትሉኝ ግን ብዙ ጊዜ ስለምቸኩል የሆነ ነገር እየበላሁ ጉዞ ጀምራለሁ :: ታዲይ ኢትዮጲያ ቢሆን ከ "አያፍርም ወይ " እስከ "ቡዳ ይበላሀል " የማይባለው ነገር የለም ::
ሌላው የገንዘብ አያያዛቸው ይመቸኛል። sconto ያለበት ሱቅ ሲያፈላልጉ ለጉድ ነው :: የሌላውን ባላውቅም ጣሊያኖች በዚህ የሚችላቸው ያለ አይመስለኝም :: አንዱ ኢንዶኔዥያዊ ጉዋደኛዬ የማያውቀው (በቅናሽ የሚሸጥበት) ሱቅ የለም :: እኔ ደሞ አሳ በጣም ነው የምጨፈጭፈው:: እና ልጁን "ባክህ ዓሳ ርካሽ የሆነበትን ሱፐር መርካቶ ነገረኝ " ስለው "ምን አይነት ዓሳ ነው የምትፈልገው " አለኝ :: እንግዴ ይታያችሁ ምን ያህል እንደሚያውቅ።



“ኢትዮጵያን እንርዳት”

ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ
30/07/2009

……....ባለፈው ሣምንት በቦሎኛ ዩኒቨርስቲና በአዲስ አበባ፣ በወለጋ፣ በመቀሌ ዩኒቨርስቲዎች መካከል በጋራ ሊያሰራቸው የሚያስችልና ረጅም ጊዜ የፈጀውን ክፍል አንድ ሳይንሳዊ ስምምነት ለመፈራረም በቅተዋል:: ስምምነቱንም የፈረሙት እያንዳንዱን ዩኒቨርስቲ በመወከል በመሥራት ላይ የሚገኙት የየዩኒቨርስቲዎቹ የዲን ሃላፊዎች ሲሆኑ ይህ ፕሮጀክት ለጊዜው ሁሎችንም የትምሕርት ክፍሎች ሙሉ በሙሉ ያጠቃለለ ሳይሆን የተወሰኑትን የትምህርት ዘርፎች ብቻ የሚመለከት ይሆናል::

……....የአዲስ አበባና የቦሎኛ ዩኒቨርስቲ ስምምነት በታሪክ ትምህርት ላይ ያተኮረ ሲሆን በወለጋና በቦሎኛ ዩኒቨርስቲ መካከል ደግሞ የእርሻ ትምህርትን ይመለከታል:: በመቀሌና በቦሎኛ ዩኒቨርስቲ መካከል የተፈረመው ስምምነት ግን በሕግ ትምህርት ላይ ያተኮረ ይሆናል::

……....ምንም እንኳን ሃሳቡን የሰነዘርኩትና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ እኔ ብሆንም ይህ ስምምነት ከግብ ሊደርስ የቻለው ከእትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች በኩል በተባበሩኝ እትዮጵያውያንና ከቦሎኛ ዩኒቨርስቲ በኩል ደግሞ ደከመን፣ ሰለቸን ሳይሉ ተስፋቸውን ባለመቁረጥ እስከመጨረሻ በትዕግስት አብረውኝ በሰሩት የሙያ ባልደረባዎች ተባባሪነት በመሆኑ ሁሉንም በዚህ አጋጣሚ ላመሰግን እወዳለሁ::

zeleke_eresso@yahoo.it



ለማርኮ በየነና ለቤተሰቡ ወገናዊ የድጋፍ ደብዳቤ

የጣሊያን ዘረኞች ባይወዱትም ይስሙት

……....ሰሞኑን ናፖሊ ተብላ በምትጠራው አንዲት ታሪካዊ የጣሊያን ከተማ ውስጥ በማርኮ በየነ (አባቱ በትውልድ ኢትዮጵያዊ) የዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስ ተማሪ ላይ የተፈፀመውን ዘረኝነት የድብደባ ሙከራን አስመልክቶ የተፃፈውን ባነበብኩበት ወቅት በልጅነቴ የሰማሁት አንድ ነገር ትዝ አለኝ:: ነገሩም አያቶቻችን ይናገሩት የነበረው “ጣሊያኖች ፋሺስቶች ናቸው” የሚለው ተራ መሰል አባባል ነበር:: ይህም አነጋገር መሉ በሙሉ እውነትን ያዘለ ነው ብሎ ባይባልም መሉ በሙሉ ከውነት የራቀ ነው ለማለት ግን እጅግ በጣም ያዳግታል:: በተለይም በነዚህ በመጨረሻዎቹ አመታት አካባቢ በጣሊያን አገር ውስጥ ማለትም እንደተቀሩት የአውሮፓ አንዳንድ ከተሞች ሁሉ በውጭ አገር ዜጋው በተለይም በአፍሪካውያን ላይ ከቃላት ዘለፋዎች አልፎ ተርፎ የድብደባ ሙከራዎች በተግባር ሲከሰቱ ማየት ከተጀመረ ሰንበት ብሏል::

……....ለነገሩ ጣሊያናዊ ሁሉ ፋሺስት ወይም ተደባዳቢ እንዳልሆነ በሚገባ አውቃለሁ; ጥቂት “ነጭ የበላይ ነው” የሚሉ እብድ ውሾች የአያቶቻቸውን ፋሺስታዊ አመለካከት እስካሁንም ያልተላቀቁ ሁሉ እራሳቸውን ቀና ቀና በማድረግ ህብረተሰቡ ለጦርነት እንዲነሳ የቅስቀሳ ሙከራቸውን በመዘርጋት ላይ ስለሆኑ “ቆማጣን ቆማጣ ካላሉት ገብቶ ይፈተፍታል” የሚለውን የአባቶቻችን ተረት ማስታወሱ ለወደፊት ሊጠቅም ይችላል ባይ ነኝ::

……....በማርኮ በየነ ላይ የተፈፀመው ድብደባ ቁስሉ ከነገ ወዲያ ታክሞ ይድናል; ታክሞ የማይድነው ቁስል ግን ቢኖር ለምን? ምን አድርጌ ነው? እና ለመሳሰሉት ጥያቄዎች መልስ ከማጣት የተነሳ በውስጥ የሚፈጠረውና መልስም የማይገኝለት የጨንጓራ በሽታ ነው:: ይህ ለሁላችን እንደምሳሌ ልንወስደው የሚገባ ትምህርት ሊሆን ይችላል ብዬ በመገመት ለማርኮና ለቤተሰቦቹ በዚህ አጋጣሚ ካጠገባችሁ ነን ብዬ በማለት ደህና ሁኑ እላለሁ::

ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ
Zeleke_eresso@yahoo.it




"በወጣቱ ማርኮ በየነ ላይ የተፈጸመበት ወንጀል ከዘር ማጥፋት ወንጀለኛነትና ጥቃት ጋር የተያያዘ ነው" (አባቱ ፕሮፌሰር ያቆብ በየነ)
09 03 09

……....ማርኮ በየነ ነዋሪነቱ ናፖሊ፣ ትውልዱ እዚሁ ጣሊያን፤ አባቱ ኢትዮጲያዊ እናቱ ጣሊያናዊት የሆኑ የ22 ዓመት ጎልማሳና የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነው። ከትናንት በስቲያ በተለመደው ቦታ ከጓደኞቹ ጋር በዋለበት የናፖሊ መሀል ከተማ ውስጥ የሚገኘው ፒያዛ (Piazza del Gesù) አካባቢ ዘረኝነትን ቤሚያራምዱ ግለሰቦች ስላደረሱበት በደል የጋዜጣዊ መግለጫ አድርጓል። በቃለመጠይቁ ላይ ከሰጠው መልስ ላይ “ከዚህ ጥፋ!! ቆሻሻ ባሪያ…!!” እያሉ እንደዘለፉትና ይባስ ብለውም ጥቃት እንደፈጸሙበት ሁሉ አብራርቷል። የማርኮ ቤተሰቦችም ይህንን ጉዳይ በሚሰማ ፍ/ቤት ክስ የሚያቀረቡ ከሆነ መሠረታዊ አዝማሚያው በወጣቱ ላይ ያደረሱበትን ጥቃትና የዘረኛነት ወንጀል ዝንባሌ ላይ የሚመረኮዝ ይሆናል ተብሎ ይገመታል። በዘር ማጥፋት ወንጀለኛነት እና በተሰነዘረበት ጥቃት ላይ ከተመረኮዘ ችሎቱ በቀጣይ መታየቱ የማይቀር ስለሆነ በአንክሮ እንከታተለዋለን።

……....ከዚህ በታች የሰፈረው ጽሁፍ የዩንቨርስቲ መምህር የሆኑት አባቱ ፕሮፈሰር ያቆብ በየነ እና ለጥቃቱ ሰለባ የሆነው ልጃቸው ማርኮ በየነ በጋዜጣው ላሪፑብሊካ (La repubblica) ቃለመጠይቅ ላይ የሰጡትን ምላሽ የሚያሳይ ነው። ፕሮፈሰር ያቆብ በየነ በጋዜጣ መግለጫ መልሳቸው ላይ “ዘረኝነት በዚህ ዕድሜዬ ማየቴ እና ከዚህ በፊት ምንም አይነት የዘር መድልዎ ያልተፈጸመባት ናፖሊ ውስጥ አሁን መከሰቱ እጅግ አሳዝኖኛል” ብለዋል። ይህ ጋዜጣዊ መግለጫ የወደፊቱ እርምጃቸው ምን እንደሚሆን ይዳስሳል።

አብራሃም ዘውዴ (ቦሎኛ)






አሳዛኝ ዜና!

……....በጀልባ ውቅያኖስን በማቋረጥ ወደ ጣሊያን ለመግባት በአደረጉት ሙከራ ቁጥራቸው 75 የሆኑ ኤርትራውያን ህይወታቸዉን አጡ። እነዚህን ስደተኞች ይዛ ከሃያ ቀን በፊት ከሊቢያ ከተነሣችው ጀልባ ነዳጅ አልቆባት ሲሲሊ ካናል ውስጥ ለብዙ ቀኖች ቆማ እንደነበረና በሕይወት ማግኘት የተቻለው 5ቱን ብቻ እንደሆነ ነው። ከእነዚህም ሁለቱ ከፍተኛ የጤና ችግር ላይ በመሆናቸው ሕክምና እየተደረገላቸው መሆኑን ተጠቁሟል።

……....እስካሁን ባህር ውስጥ ከተጣሉት ግለሰቦች ሬሳቸው መገኘቱ በየትኛውም የዜና ምንጮች አልተዘገበም። በኣጠገባቸው ያልፉ የነበሩ መርከቦች እርዳታ የመንፈግቸውም ጉዳይ ዋናው ምክንያት የጣሊያን መንግስት በመርከበኞች ላይም ሆነ በባህር ዳር ጠባቂዎች ላይ በተለያዩ ሁኔታዎች ተጽዕኖ በማሳደሩ ነው ተብሎ ይገመታል፡፡ ጉዳዩ ዝርዝር ውስጥ ሳንገባ ነገሩ ይህን ያህል አስደንጋጭ የሆነው ለምንድነው? ቢባል የኛው ወገን መሆናቸው ብቻ ሳይሆን የአሟሟታቸው ሁኔታ ነው። በአንድ ጊዜ ጉዞ ብዙ መሞታቸውና ወደ ባህር መጣላቸውን፣ ለሞታቸው ምክንያት የሆነው ደግሞ በጥማት የባህሩን ውሃ ከጠጡ በኋላ በጠና እየታመሙ መሞታቸው ነው። በአሻጋሪዎቻቸው ተደብድበው ለሞት የተዳረጉም ሊኖሩ ይችላሉ” ብለው አንዳንድ የጣሊያን ህትመቶች ጥርጣሬያቸውን ጠቁመዋል።

……....መቼም ይህ ዜና የዘገነነና ጨካኝ በመሆኑ ብዙዎቻንን እያነጋገረን ይገኛል። ከምንገናኛቸው ወገኖች የመጀመሪያው ርዕስ አድርገን የምንጨዋወተው ይኽንኑ ሆኗል። ሁላችንንም ለጊዜው ሀዘን፣ ንዴትና ቁጭት፣ እልህና ወኔ ቢፈታተኑንም እንደየእምነታችን ልንጸልይላቸው ይገባናል። ከዚሁ ጉዞ በህይወት የተረፉትም እንኳን በጣሊያን ሀገር የተለመደው የስደተኞች መብት ችግር ላይ እንዳይወድቁ እንዲሆንላቸውይገባል። ማለትም በቅርቡ ጣሊያን በአፀደቀችው ሕግ ከአምስት እስከ አስር ሺህ ዩሮ ይቀጡና ተመልሶ ወደየመጡበት የመባረራቸው ሁኔታ ስለአለ ይህ ደግሞ እንዳይደርስባቸው የሕብረት ድምጻችንን ማሰማት የሚቀጥለው ተግባራችን ሊሆን ይገባል።

……....ሰለጠነ የምንለው ኅብረተሰባችን ገሃድ በሆነ ሁኔታ የውጭ ዜጎችን ያለመቀበል ስሜት እያሳደገ መምጣቱ ይታያል። ይህም ሌሎችን ካለማወቅ የመጣ ብቻ ሳይሆን የራሳቸውን ለሌሎች ላለማካፈል ወይም ከአጉል ራስ ወዳድነት የመነጨ ነው። ምንም እንኳን መንግሥታት ስደትን የመቆጣጠር ሕጋዊ መብት ያላቸው ቢሆንም ስደተኞች ደግሞ የመዳንና አስቸኳይ ርዳታ የማግኘት የማይገርሰስ ሰበአዊ መብት አላቸው። ይህን መሰል አሳዛኝ ሁኔታዎች እየተደጋገመ ስለሚከሰቱ ይህንን የሚመለከት ጥብቅ የዓለም አቀፍ ፖሊሲ ያስፈልጋል ባይ ነኝ።... ከዚህም ላይ ተደምሮ ጸጥ ያለው የምዕራባዊያን ግድየለሽነትና ግድየለሽነት (indiferenza)...

አብራሃም ዘውዴ (ቦሎኛ)
22 08 2009


.

የበረሀውን ሳይሆን የባህሩን

……....የቅጽል ስሜ ደፋሩ ይባላል። በሃያዎቹ የእድሜ ክልል ውስጥ እገኛለሁ። ረጅሙንና የበረሀውን ታሪክና ጉዞ ወደ ኋላ እንጨዋወተዋለን። ለአሁኑ በጀልባ ላይ ሆኜ ያየሁት አሳር እና አበሳ በአጭሩ።

……...." ገና ከመነሻችን ላይ ጀልባውን የሚነዳውና የሚቀዝፈው ከእኛው መካከል መሆን እንደነበረበት ሲነግረን በጣም ነው የተደናገጥነው። ነገር ግን ምንም ምርጫ አልነበረንም። ቀዛፊው ደግሞ አሣ አጥማጅ ከመሆኑ በስተቀር ሌላ የሚያውቀው ስላልነበር ሁኔታው ለአደጋ የሚያጋልጠን ነበር።

……....ሕልሜን እውነት ለማድረግ 30 ከሚሆኑ ወጣት ጋር በእንጨት ጀልባ ተሳፍሬ ጉዞዬን ቀጠልኩ። የተሳፈርኩበት ጀልባ በምስማር በተመታ እንጨት የተሠራ ነበር። ርዝመቱ 5 ሜትር ነው። ጎኑ ደግሞ ያው ያበጠ ቅርፅ ስላለው መለኪያ የለውም። ባሕሩ ላይ እንዳለን የደረሰው ማዕበልና ሞገድ እጅግ ከባድ ነበር። ሞገድ በተነሳ ቁጥር ጀልባዋ በውሃ ስለምትሞላ ውሃውን እየጨለፍን ወደባህሩ ብንጨምርም ማዕበሉ መልሶ ስለሚያለብሰው ያገኘን ስቃይ ከ-እሰከ ተብሎ አይነገርም። ቅዝቃዜው አጥንት ውስጥ የሚገባ ነው። ሌሊትማ ያለው ቁር አያድርስ ነው። ሁልጊዜ ደግሞ እርጥበት ስለማይለየን ቆፈኑ አያላውስም። በውንም በህልምም የምንናፍቀው የሞቀ ልብስ መልበስ ነው። መተኛት የሚባለው ነገርማ እንደው የማይታሰብ ነው። ከዚህ ሌላ በጀልባው ውስጥ ያለው ቦታ ጠባብ ከመሆኑ የተነሳ እግር ዘርግቶ መተኛት አይቻልም። መቀመጫዎቹ ደግሞ ጠባቦች ነበሩ።

……....በሁለተኛው ቀን በዲዝል ሞተር የሚንቀሳቀሰው ጀልባ ቆመ። ሞተሩ በመጥፋቱ ሊንቀሳቀስ አልቻለም። ግማሽ መንገድ ላይ ያሰብንበት ሳንደርስ ባህር ውስጥ ልንሰጥም ነበር። ሆኖም ሌላ መልካም ዕድል ስለአጋጠመን የባህር አሳሽ መርከብ ደርሶ እኔንና አብረውኝ የተሳፈሩትን ጓደኞቼን ሊያተርፈን ችሏል። ምንም እንኳን ሁሉም ነገር አደገኛ ቢሆንም በሶስት ሌሊትና በአራት ቀን ጉዞ ከተመኘሁት ቦታ ደርሼአለሁ። አራት ቀን ሙሉ በአደረግንው ጉዞ የአትላንቲክ ባህርን አቋርጦ ላምፔዱሳ ደረስኩ። እንደዚህ ያለውን ሁኔታ በሕይወት ዘመኑ እንደማልደግመው እርግጠኛ ነኝ። በእርግጥ እንደዚህ መሆኑን ባውቅ ኖሮ የማልሞክረው እንደነበርና እኔን ያየህ ተቀጣ የሚያሰኝ መሆኑን ልነግራችሁ እወዳለሁ።

……....ለምን ወደ ጣሊያን መምጣት እንደፈለግሁ
…….... “በቤታችን ምንም ገንዘብ የለንም። እኔ የምፈልገው ሠርቶ ገንዘብ ማግኘትን ነው። በቀላሉ ለመናገር እኔ የምፈልገው ቤተሰቤን መርዳት ብቻ ነው። ምንም ይሁን ምን፣ የትም ይሁን የት ሥራ አግኝቼ መሥራቴ ነው ለእኔ ዋና ቁም ነገር። የሥራ ምርጫ በእኔ ዘንድ ቦታ የለውም” የሚለው ወጣት ደፋሩ ህልሙን እውን ለማድረግ ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍሏል።
……....በጀልባ እያሳፈሩ በሕገ ወጥ መንገድ ወደ አውሮፓ ለሚያስገቡ ነጋዴዎች አንድ ሺህ አምስት መቶ ኤውሮ እንደከፈለ ቢናገርም ገንዘቡን እንዴት እንዳገኘው ለመናገር ፈቃደኛ አልሆነም። የጀልባው ባለቤት አንድ ሺህ አምስት መቶ ኤውሮ እንደተቀበለው ተናግሯል። ይህ እንግዲህ ከእያንዳንዱ ተሳፋሪ መሆኑ ነው። ይህን ያህል ገንዘብ የሚጠይቀውም ጀልባውን ለመሥራት እንደሆነ ይነገራቸዋል። ታዲያ ይህ ገንዘብ ምግባቸውን ስለማይጨምር እያንዳንዱ የራሱን ምግብ መያዝ ነበረበት። ከዚህም ሌላ ጀልባውን የሚያንቀሳቅሰውን ሞተር ተሳፋሪዎቹ እራሳቸው መግዛት ነበረባቸው። ... ይቀጥላል ...

……....ከአራት ቀን ጉዞ በኋላ የደሴቷ ወደብ ደርስኩ
……....ስለ ወደፊት ሕይወቴ ምንም የማውቀው ነገር የለም። ስለዚህም ያለኝ ፍርሃት ከፍተኛ ነው። የቀይ መስቀል ከመጸወተኝ አሮጌ ልብስ ሌላ ምንም የለኝም። ወደ አውሮፓ ብገባም የተመኘሁት ሁሉ አልተሳካልኝም። መንግሥት ወደሀገሬ እንድመለስ ወስኖብኛል። መሥራትም አይፈቀድልኝም። እንዲያውም የስደተኞች ማጎሪያ ጣቢያ መቀመጥ ነበረብኝ። የትም መውጣት ስለማይፈቀድልኝ ያው እስረኛ ማለት ነው። እኔ መቼም ወደ ሃገርህ መመለስ አለብህ የሚሉኝ ሁኔታ በምንም መልኩ የማላስበው ነው። ከሃገር ስወጣ ለወላጆቼ ምንም የነገርኳቸው ወይም ያማከርኳቸው ነገር አልነበረም። ከደረስኩ ከሃያ ቀን በኋላ ግን በስልክ እንዳገኘኋቸውና መልካም ዕድል እንደገጠመኝ ስለነገርኳቸው ሁሉ ነገር ቀለል ብሎላቸዋል። ይሁንና የአውሮፓው ክፍለ ዓለም አንፈልግህም እንደሚለኝ ለወላጆቼ መግለጽ አልፈልግም። ከሁለት ያጣ ጎመን የሚያሰኝ ሆኖብኛል። ... ይቀጥላል ...

……....ከአካባቢው ስለዚሁ የሚሉት አላቸው
…….... “እኔ ፖሊስ ነኝ ሥራዬም በአውሮፓ ኅብረት የተቋቋመውን የአካባቢውን ጣቢያ በኀላፊነት መምራት ነው። ሃያ አራት ሰዓት ሙሉ እረፍት የለኝም ማለት ይቻላል። የስደተኞች ችግር በፖለቲካ እስካልተፈታ ድረስ ችግሩ የሚያቋርጥ አይደለም። ብዙ የሥራ ባልደረቦች ቢመደቡልኝም ሥራው የሚገፋ አይደለም።”እኒህ ያካባቢው አዛዥ የሆኑት ፖሊስ ስለ ስደተኞች ያላቸው አመለካከት የሚወቀስ አይደለም ለሰብአዊ መብት ክብር ይሰጣሉ። እንደሚናገሩት እነዚህ የአፍሪቃ ስደተኞች ሰው አክባሪዎች ማንንም ማስቀየም የማይፈልጉ ናቸው። የተማሩም አሉባቸው። የመጡባቸውን አገሮች ለመጎብኘት አሳብ አላቸው። መጽሓፍ ገዝተው በማንበብ ላይ ናቸው። ወጣቶቹ ለምን እንደሚሰደዱ ማወቅ እፈልጋለሁ። የተማረውና ወጣቱ ትውልድ አገሩን እየለቀቀ ለስደት መዳረጉ ግንዛቤ እንዲኖረኝ እፈልጋለሁ ይላሉ። ወጣቱ ትውልድ አገሩን ጥሎ ከፈለሰ ችግር አለባቸው። ይህንን ችግር በየትውልድ አገራቸው ሊፈታላቸው ይሚችል ሁኔታዎች መደረግ ግዴታችን መሆን ይገባዋል። ... ይቀጥላል ...
……....ለማጠቃለያ ያህል
……....
ስደተኞች ያሰቡበት እስኪደርሱ የሚደርስባቸው ችግር በቃላት ተዘርዝሮ አያልቅም።
……....ባህሩን በትንሽ የእንጨት ጀልባ አቋርጠው ከአሰቡበት የሚደርሱት በአሥር ጀልባዎች ከተሳፈሩት ውስጥ አራቱ ናቸው የሚደርሱት። ወጣቶች የአትላንቲክ ውቅያኖስን አቋርጠው ወደ አውሮፓ ክፍለ ዓለም በሚያደረጉት ሙከራ የሚደርስባቸው የማዕበልና የሞገድ ችግር ይህ ነው ተብሎ በቃላት መግለጽ አይቻልም። እነዚህ ወጣቶች ለዚህ ሁሉ ስቃይ የሚዳረጉት በሕጋዊ መንገድ ወደ አውሮፓ ክፍለ ዓለም መግባት ስለማይችሉ ብቻ መሆኑ ይታወቃል። የቱሪስት የጉዞ ሰነድ ወይም የሥራ ፈቃድ አግኝቶ ከአገራቸው መውጣት አይችሉም። እነርሱ የሚያስቡት በምንም መልኩ አውሮፓ ከደረሱ ሁሉ የተቃና፣ መልካም ዕድል እንደሚገጥማቸው፣ የአውሮፓ ኑሮ የገነት ኑሮ እንደሆነ፣ ወዘተ ... አድርገው ነው የሚያስቡት። ... ይቀጥላል ...
ሌላው ደግሞ ፈረንጅ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ ይከበራል፡፡ እኛ ግን አሁን አሁን ወደ ምዕራብ ስንመጣ እንናቃለን። ብዙዎቻችን የአገሩ ዜጋ የማይፈልገውን ስራ እንሰራለን፡፡ ምሁሮችም እንኳን ብንሆን የኑሮ ጉዳይ ስለሆነ እራሳችንን ዝቅ አድርገን ያልፈለግነውን ስራ እንሰራለን፡፡ ያልጠበቅነውና ያልተመኘነው ህይወት ውስጥ እንኖራለን፡፡ በአጠቃላይ ብዙዎቹ ኢትዮጵያውያት ስደተኛ እህቶቻችን ያልፈለጉትን የጠረጋ ሥራ፣ ያልተመኙትን የሰው ቤት ሥራ ... ወዘተ ... ነው የሚሰሩት፡፡ የአውሮፓ ሀገሮችም ቢሆኑ በትናንሽ ጀልባዎች እየተሳፈሩ የሚገቡ ስደተኞችን እንዴት ማስቆም እንደሚቻል ግራ የገባቸው ይመስላል። ማንም ሰው በባህር ላይ አጥር ማጠር ስለማይችል ሁኔታው በቀላሉ የሚታይ ሆኖ አልተገኘም። ... ይቀጥላል ...
……....የበጎ አድረጊዎቹ ምክር ...
የሞቱ ሰዎች አስከሬን ባህር ላይ ሲንሳፈፍ በማውጣት የተሰባበሩ ጀልባዎችን ሰብስቦ በመከመር የሚያገለግሉት የበጎ አድረጊዎች ምክር ...
ስደተኞችን የመግታት እርምጃ መውሰድ ብቻ ሳይሆን አሁን አሁን አስፈሪ መሆኑንና አማራጩን ጭምር ነው የምንጠቁመው። ህይወትን ለማትረፍ ካልሆነ በስተቀር የተሻለ ኑሮ ለማግኘት ብሎ በህገወጥ መሰደድ ይቅርባችሁ። ፀፀት ውስጥ እንዳትገቡ። በዚያው በትውልድ አገራቸው ብትኖሩ እንደሚሻል አትጠራጠሩ።
* አውሮፓ ገነት ናት" የሚለውን አጉል አስተሳሰብ እንድታስወግዱትና ተጨባጩን ሀቅ እንድታውቁት ለማድረግ፣
* አውሮፓ ውስጥ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ሳያገኙ በመሸቀል ብቻ ኑሮን መግፋት የቱን ያህል እንደሚያደክም፣
* በቅርብ ጊዜ ከመጡት አፍሪካዊያት እህቶቻችን የነበራቸው ህልምና ገሐዳዊው ይዞታ ፍጹም የተለየ ሆኖባቸው በሴትኛ አደሪነት የተሠማሩ መሆናቸውን፣
* ...............................
* ...............................
ይህንንም በመገንዘብ ሐቁ ያልታያችሁ እንዲታያችሁ ይሁን። ... ይቀጥላል ...



ማህበራዊ ኑሮአችን በጣሊያን


አብራሃም ዘውዴ


……....ሰላም... አንድ ሰሞን "ለወገን ደራሽ ወገን ነው" የሚል አባባል እሰማ ነበር። ለእኔም ቢሆን አብራችሁኝ የውጪውን ሕይወት ፅዋ ከምትካፈሉት በስተቀር ማን ሊደርስልኝ። ችግሬንም ብሶቴንም አምቄ እስከመቼ? እናም የይሉኝታንና የሀፍረትን ድር በጣጥሼ ገበናዬን አውጥቼ ላጫውታችሁ። ግን ችኩል ፍርድ አትስጡኝ። ስህተቴንና የጥፋቴን መነሻዬን እንዲሁም መድረሻዬን አጢናችሁ ምክራችሁን ብትለግሱኝ ብዬ ነው።
በጣሊያን ለምንኖረው አበሻ…
……....1/ የአስተሳሰብና የአብሮ የመኖር ገጽታችንን ለማሳየት
……....2/ ከሌሎች የአውሮፓ ሀገሮች ካሉት ጋር በማነፃፀር የውጪ ሀገር ሕይወታችንና አኗኗራችን ለማሳየት
……....3/ ስለማህበራዊ ችግሮቻችን በጨረፍታ በማቅረብ ለወደፊት በጎ ራዕይ የሚያሳየንንና የሚበጀንን ወቅታዊ መፍትሔዎች ለመጠቆም
……....4/ በጣሊያን የውጪ ሀገር ዜጎችን በሚመለከት ወቅታዊ ችግሮችን በመዳሰስና ለውይይት ለማቅረብ
……....5/ የውጪው ህይወታችን ምን እንደሚመስል ግንዛቤ ለማድረግና ራሳችንን ለማስተዋል ...
……....6/ እኔንም ከገጠሙኝ ጨማምሬ በማውጋት በዛው ላይ የግሌን አስተያየት አያይዤ ለማከል
……....7/ ... ይቀጥላል ...
……....ለነገሩ የጣሊያን ሀገር ኑሮውን እዚህ እያለን ስለምናውቀው ከዚህ ጽሁፍ ብዙ አዲስ የሆኑ ነገሮችን አታገኙበትም። ግን "ያለውን የወረወረ ፈሪ አይባልም" ይባል የለ! እናም ወደ ቁም ነገሩ ላምራ። መንደርደርያ ይሆነኝ ዘንድ ከዚህ በታች አንዳንድ ጥያቄዎችን አስፍሬ መልስ በመስጠት ለመጀምር ሙከራ ላድርግ።
……....* እኛ በምንኖርበት የባዕድ ሀገር ህዝብ ባህል፣ ቋንቋ፣ ምግብ፣ አየር... ተላምደንና ተውህደን መኖር እንችላለን ወይ?
……....* በማህበራዊ ሁኔታዎችስ ምን ላይ እንገኛለን?
……....* ምን ይጎለናል?
……....* በቁጥርስ ምን ያህል እንደርሳለን?
……....እንዚህን ጥያቄዎች ሙሉ በሙሉ መመለስ ባልችል እንኳን እዚህ ያለነው በሙሉ ጠያቂና ዘመድ የሌለን ባዕድ ሀገር ውስጥ ብቻችንን የምንኖር፣ ወዳጃችን ሥራችን ብቻ መሆኑን እናውቀዋለን። በጣሊያን ቁጥራችን ከ20 ሺህ በላይ እንሆናለን ተብሎ ይገመታል። ሚላኖና ሮማ በቁጥር ብዙ ናቸው። በነዚህ ትላልቅ ሀገር በብዛት የሚኖሩበትን ቦታ "አበሻ ሰፈር" ተብለው የሚጠሩ ቦታዎችም አሉ። እኔ ባለሁበት ክፍለ ሀገር ምን ያህል እንዳሉ ሲነገርም ስላልሰማሁ ወይም ተጽፎ ስላላነበብኩ በግምትም እንኳን ይሄን ያህል እንደርሳለን ለማለት አስቸጋሪ ይሆንብኛል። ነገር ግን ቁጥራችን በጣም እየጨመረ መምጣቱን በሚገባ አውቃለሁ። በምኖርበት ከተማ እንኳን ከዛሬ አስር ዓመት ወዲህ በቁጥር እጥፍ ድርብ ጨምረናል የሚል ግምት አለኝ። ... ይቀጥላል ...
……....ታዲያ ለብዙዎቻችን መገናኛ የሚፈጥሩልን ዓመታዊ ክብረበዓላችንን ወይንም አውደዓመት ላይ የሀገር ምግብ ሰርተን፣ ቡናውን አፍልተን፣ ቄጤማና ሳር ባይገኝም ምንጣፉንም ቢሆን በመሬት ላይ አንጥፈን እንሰባብሰባለን። ሌሎች መገናኛ ሁኔታዎችን ከሚፈጥሩልን መካከል ለምሳሌ - በሰርግና በልደት፣ በችግርና በሀዘን ወዘተ ... ናቸው። በየቤታችንም በመገባበዝ እንገናኛለን። ኦሪጂናል የሀገራችንን ምግቦች እዚህ ለማግኘት ባንችልም እንኳን አእምሮታችንን ለመወጣት የፉርኖ ዱቄት እንጀራ በመጥበሻ ላይ ጋግረን ከዘመዶቻችን በሚላክልን የተፈጨ በርበሬና ቅቤ ወጥ አዘጋጅተን ባልንጀሮቻችንን ጠርተን አብረን እንውላለለን። ዳቦ በወጥ መልመድም ግድ ሆኗል። ዝነኛውንም የሽሮ ዶኬንም የማይወደው የለም። በተቃራኒው ደግሞ ከማንም ጋር ግኑኝነት የማያደርጉ በርካታ የሆኑ የተገለሉ፣ ያልታወቁ፣ የኑሮውንም ውጣና ውረድ መቋቋም ያቃታቸው፣ የብቸኝነት ስሜት ያላቸው፣ የህሊና ዕረፍት የማያደርጉ፣ ለራሳቸው የሚሆን መዝናኛ ነገሮችን እንኳን የማያደርጉ የሀገር ልጆች ሊኖሩ ይችላሉ። በመንፈስ ጭንቀት ወይም በአዕምሮ ህመም ምክንያት ብቻ ሊሠሩ ባለመቻላቸው ወደሀገር ቤት የሚመለሱም አይጠፉም። ለዚህም እንኳን የሥነ አዕምሮና የሥነ ልቦና ምክር ሊሰጥበት የሚችልበትን ማዕከል ለማግኘት የሚጠየቅበትን ሳያውቁ፣ የሚፈለገውን አገልግሎትና ህክምና ሳያገኙ ወደ ቤተሰባቸው የሚመለሱና የሚላኩ ጥቂቶች አይደሉም።
.
……....ታዲያ በጣም በተቀራረቡት ወይም በደንብ ከሚግባቧቸው ጓደኛሞች መሀከል ልዩ ፍቅርና ትሥሥርም አለ። ከትውልድ ሀገራችን ስለራቅን ነው መሰለኝ። አንዳንድ ግዜም ማኅበሮች ወይም ኮሙኒቲዎች በዓላት ላይ በሚያዘጋጃቸው ፌስታዎች አማካይነትም ተያይተን የማናውቃቸውንና እሩቅ ሀገር ያሉትን እንድንተዋወቅና እንድቀራረብ አድርጎናል። እናም በተገናኘንባቸው አጋጣሚዎች በሥራችን ላይ ያጋጠሙንን ችግሮች እያነሳን እንጨዋወታለን። ስለሀገር ናፍቆትና ትዝታ እናወራለን። እዚህ ሀገር ስለ እኛ በሚያስደንቁንና እንግዳ በሆንብን ነገሮች ዙሪያም እናወጋለን። እኛ የፈረንጆቹን አንዳንድ ልማድ በምናይበት ጊዜ እንደምንገረመው እነሱም ስለ እኛ ባህል እንግዳ በመሆናቸው ብተመጽዖ ሲያወጉበት አይተናል።
ለምሳሌ ያህል እ.ኤ.አ በ1995 ዓም ሀገሬ ደርሼ ስመለስ የዘመዴን ሠርግ ከቀለበት እስከ ቅልቅል ያለበትን የቪዲካሴት ፊልም ለፈርንጆች ጓደኞቼ አሳይቼ ነበር። የምግቡና የሰው ብዛት፣ የሙሽራዋ ቬሎና የሚዜዎች ልብስ፣ ከዚያም በላይ ከተማዋንና ፎቁን ሲያዩ ሊያምኑ አልቻሉም። በተለይ የምግቡና የሰው ብዛት ስላስደነቃቸው "ሀብታም ናችሁ ወይ?" ብለው ጠይቅውኝ ነበር። "በሀገራችን ሀብታምም ሆነ ድሀ ልጁን ሲድር እንደዚህ ደግሶ ነው" ብዬ ነገርኳቸው። ጥሎሽ፣ መልስ፣ ቅልቅል እየተባለ ሲጨፈር፣ ሲበላና ሲጠጣ ሲያዩ ድሀ ብለው የደመደሙላት ሀገራችን ሳትደንቃቸው አለቀረችም። ጥሬ ስጋም እየተጎረደ ሲበላም አይተው በጥም ተደንቀዋል። እግረ መንገዳቸውን የእነርሱን ሁለት ሰዓት የማይፈጅ የሰርግ ዝግጅት እና ያለጥሎሽ እንዲያገቡ የሚያደርገውን ባህላቸውን ረግመውታል። ይህንንን ማለቴ ሀገራችን የተትረፈረፈባት ነች ብዬ ጉራ ለመንዛት አልነበረም። እንደው የእነሱ አመለካከት የተለየ በመሆኑ እንዲያስተውሉ ለማሳወቅ ነበር። እዚህ ላይ ሀገሪቱ የምትገኝበትን ችግር፣ ድህነት፣ የረሃብና የድርቅ ሁኔታዎችን በየጊዜው የሚስሙትን ከነበራቸው ሃሳብ ጋር ቅራኔዎችን አፍልቆባቸው ስለነበር በመሀሉ ብዙ ነገር ተጨዋውተናል።
……....ለማንኛውም እኔ ከተገነዘብኩት ነገር ጣሊያኖች ብዙ ነገሮችን አቅልለው የመመልከት ልምድ አላቸው። እኛም ብንሆን ከእነሱ በአንዳንድ ነገሮች ላይ መልካሙን ባህላቸውን ለይቶ መውስዱ ሊበጀን ይችላል ለማለት ነው። ... ይቀጥላል ...
……....አንዳንድ ጊዜ ፈረንጆቹ "ዘርህ ምንድነው? ከየት መጣህ? አሳማ ትበላለህ ወይ? ወዘተ ..." እያሉ ይጠይቁኛል። በዚህ አጋጣሚ ልቤ በኢትዮጲያዊነት ስሜት የተሞላ በመሆኑ ከመልሴ ጋር አያይዤ ሌላም ብዙ ነገር እንዲያውቁ ብዬ ጨማምሬ ሳወራላቸው በተመጽዖና በመገረም ያዳምጡኛል። ለምሳሌ - 13 ወር እንዳለን፣ ከ200 በላይ ፊደል እንዳለን፣ ያለንበት ዓመተምህረት በ7 ዓመት ወደኋላ እንደምንገኝ፣ ከ80 በላይ ቋንቋዎች እንዳሉን፣ ...ወዘተ ... ሌሎችንም እንደዚሁ ሳወራላቸው በቃ ግርም ነው የሚላቸው። ማንኛውንም ነገር ስለሀገራችን ለማወቅ አስተውለው ሲያዳምጡኝ፣ ሲጠይቁኝ፣ ከልብ አድናቆትን ሲያደርጉ በጣም ደስ ስለሚሉኝ አከብራቸዋለሁ።
በተቃራኒው ደግሞ የአንዱ ሀገር ባህል ልምድና ኑሮ ሊለያይ የሚችል መሆኑን መገንዘብ የማይችለውና ያልተማረው ክፍል ተነስቶ ማንነቴን ሳያውቅ እኔን የመናቅና የማይሆን ድርጊት ከፈጽመብኝ በመናደድ ሳይሆን በራሱ አይን እያየሁት ትክክለኛውን መልስ እሰጠዋለሁ። ልሳሳት እችላለሁ ግን ጥቂቶችና ባልተማሩት ነጮች አካባቢ በእኛ ላይ የመሰልቸትና የእምነት ማጣት ሁኔታዎች ያሳያሉ።
……....እናም እኔን ከገጠሙኝ ነገሮች አንዷን ላጫውታችሁ እስቲ!!
……....እኔና የሥራ ጓደኞቼ ወደ ከተማ ወጣ ብለን ለመዝናናት ፈልገን አንድ ቡና ቤት ገባን። ታዲያ ወዲያው እንደገባን አንዷ ጣሊያናዊት እኔን ለይታ በትህትና ሳይሆን በንቀት እኔን sei di colore? ብላ ጠየቀችኝ። እኔም ቋንቋቸው እየተለመደ የመጣ ቃል በመሆኑ ብዙም ደንታ ስለሌለኝ የኔ ምላሽ "አዎ" ነበር። Di Colore ትርጉሙ "ቀለም ያለው ወይም የቀለመ" ማለት ነው።ግን ጥያቄዋ የንቀት በመሆኑ ስለከነከነኝ ብቻ ቀጥል በማድረግ Se sono di colore tu devi essere senza colore አልኳት። መቼም አብረውኝ የነበሩት ምን ማለቱ ብለው ሳይደነቁ አይቀርም። ብቻ ጣሊያናዊቷ ፊቷ ከመቅጽፈት ፍም ሲመስል አስተዋልኩ። አንድ ጊዜ በጥፊ ወለወለችኝ። እኔም ዞረብኝ እላችኋለው። እሷም ተመልሳ ደንግጣ እጇን አፏ ላይ ጭና ታየኝ ጀመር። ከዚያም የቡና ቤቷ ባለቤት ታውቀኝ ስለነበር አረጋጋችኝ። ለነገሩ እኔን ብትመታኝም አሷን ለመምታት እቅድም አልነበረኝም። ሊያውም ሴት በመሆኗ እንዴት ብዬ። መቼም እናንተም ለምን ዝም አልካት አትሉኝም። በማይረባ ነገር ምን ዱላ አስመዘዘኝ። ብቻ ያስደሰተኝ የሷ ፈዞ መቅረት ነው። Senza colore ተብላ የምታውቅ አይመስላኝም።
እስቲ እናንተው እራሳችሁ አስቡት። እኛ ከቀለምን የቀለማችን አይነት ምንድነው። ማንኛውም ቀለም ካለው ጋር ቆዳችንን ብናስተያየው አንድ አይነት አይደለም። Di Colore ከማለት ሌላ አይነት ቃል ቢፈልጉለት ይሻላል። ታዲያ እናንተንም Di Colore ቢሏችሁ እንደኔ አይነት መልስ አታድርጉ። ያው ቋንቋቸውና ልምዳቸው ሆኗልና። እኔም ቢሆን እኮ በንቀት ሳይሆን በትህትና ብትለኝ ይህ ሁሉ ችግር አይፈጠርም ነበር። በበኩሌ ጥቁርና ነጭ ይምንባባለውን እመርጣለሁ። ... ይቀጥላል ...
.
... ከዋናው አርዕስት እየወጣሁ ስለመጣሁ ወደመነሻዬ ልመለስ። ይህንን ጉዳይ በሌላ ጊዜ እንደምናነሳው አልጠራጠርም።
... ሰው ደካማ ጎን አለው። ከኛም መካከል የአብሮነት ጥቅም ስታስረዳው የማይገባውና የመረዳት ችሎታ የሌለው አይጠፋም። ይህንን ደካማ ጎኑን አይተን እንተወው ማለት አንችልም። ከዚህ የውጪ ሀገር ቅዠት ኑሮ ሌላ የአለው መጥፎ ፀባይና ልምድ ተደርቦበት አሻፈረኝ ቢል ብዙም አንፍረድበት። እዚህ አስካለ ድረስና ወገናችን እስከሆነ ድረስ የመኖር ትርጉም ጣዕም እንደአጣ ሆኖ መቅረት የለበትም። የሰው ሀገር ሰው ነውና መቼም ቢሆን እንደማይደላው ቢታወቅም አንዳንዴ በያዘው ባሕሪ የሚፈጽማቸውን ድርጊቶች ስናይና ስንሰማ አኛኑ ሊቆረቁረን ይችላልና ነው።
……....በተለይም ከሌሎች የውጪ ዜጎች መሀከል በጣም ጥቂት የሆኑት በሚፈጽሙት መጥፎ ድርጊቶች ምክንያት ፈረንጆቹ ከጊዜ ወደ ጊዜ በውጪው ዜጋ ላይ ያላቸው አመለካከት መጥፎ መልክ እየያዘ መምጣቱን ሳትገነዘቡ አልቀራችሁም። ሥነስርዓት የሌላቸው የተወሰኑ የውጪ ዜጎች ቅሚያና ድብድብ ላይ ስለሚገኙ እኛም ተደምረን ከሕብረተሰቡ እያራቀን ይገኛል። ለምሳሌ የዛሬ 10 ዓመት ፈረንጆቹ ሌባ ይሰርቀኛል ብለው አይፈሩም ነበር። ዘወትር በሚያዩት፣ በሚሰሙት፣ በሚደርስባቸውና በሚያጋጥማቸው ህገወጥ ድርጊቶች አማካይነት እኛንም በነሱ አይን እንድንታይ አድርጎናል። አንዳዶቻችንም አጋጣሚ ሆኖ አንዱ የውጪ ዜጋ መጥፎ ድርጊት በፈጸመበት አካባቢ በመገኘታችን ብቻ እንኳን አፍረት እንዲሰማን ሆነናል። ቢሆንም ሕገወጥና ማህበረሰቡ ከሚያገልለው ሁነታዎችን እስካልፈጽምን ድረስ፣ ስርዓትን አክብረን እስከኖርን፣ ከመጥፎ ልምዶች እስከራቅን ድረስ ምንግዜም ተከብረን እንደምንኖር ጥርጥር የለኝም።
በእርግጥም እኛ ኢትዮጲያዊያን ሕግንም ሰውንም በጣም እናከብራለን። የሀገሬ ልጅ ቁጡ፣ ብርቱና አትንኩኝ ባይ ነው። ሲነኩት እንደ አራስ ነብር ስለሚሆን በቀላሉ ከሰው ጋር ሊቀያየምና ሊጣላ ይችላል። ለእነዚህ አጋጣሚዎች በቅንና በጥሩ ልቦና መቅረብ ካልቻለ በኋላ መዘዞች እንዳይከተሉት በትዕግስት ማለፉ ይሻለው ይመስለኛል። ... ይቀጥላል ...
……....ክጣሊያን ወጣ ካልን ደግሞ በሌሎች የአውሮፓ ሀገር የሚኖሩት ኢትዮጲያዊያን ዜጎች በቁጥር ምን ያህል እንሆናለን። እንግሊዝ ወደ 50 ሺ፣ ጀርመን 35 ሺ፣ ስዊድን 40 ሺ፣ ወዘተ ይሆናሉ ይባላል። ሆላንድ ወይም ካናዳ ያሉት ቁጥራቸው ጣሊያን ካሉት በቁጥር የበለጡ መሆናቸውም ይነገራል። በነዚህም ሀገሮች ጠቀም ያለ ገንዘብ በሚያስግኙ አገልግሎት መስጫና የሥራ ዘርፎች ላይ ዕውቀታቸውን የሚያውሉ ብዙ ናቸው። እዚህ ጣሊያን ሀገር ግን የተማሩበትን ዕውቀት ወይም የሥራ ልምዳቸውን ተመርኩዘው ተቀጥረው የሚሠሩ ቢኖሩ ከአንድ መቶ ኢትዮጲያውያን/ት ውስጥ አንድ ቢገኝ ነው። ሁላችንም የምንኖረው በፊት ልምድ በሌሉን ሥራ ላይ ነው። የጉልበት ሥራ፣ የቤት ውስጥ አገልግሎት፣ የንጽህና፣ የህመምተኛና የሽማግሌ ጥበቃ ወዘተ ... በመሥራት ነው። በአጠቃላይ እዚህ ጣሊያን ሀገር አንድ የውጪ ህገር ዜጋ በሙያው አይደለም ሥራ የሚገባው። ተምሬአለሁና ይህንን እችላለሁ ብሎ ተወዳድሮ መግባት አይችልም። ብዙ መንከራተት አለ። ካላወቅንበት መሻሻል ቀርቶ ያለንም የሥራ ልምድም የሚያሽቆለቁልበት ሀገር ነው። ይሄ ሁሉ ሞራላችንን ነክቶታል።
አሁን አሁን ግን ነፃነት በማይሰጥበት ሰው ቤት ተወስኖ ላለመቅረትና እንደልብ ለመሆን የግል ንግድ የሚያደርጉ፣ ትንሽም ገንዘብ አጠራቅመው ምግብ ቤት፣ ፀጉር ቤት የከፈቱ፣ በአላቸው ችሎታም ሆነ ሙያ በግል በመሥራት በማደግ ላይ ያሉ ወገኖችን ማየት አሰይ" ያሰኛል። ... ይቀጥላል ...
……....በጣሊያን ስላለው ቆም ላድርግና በሌሎች ሀገር ኢትዮጲያውያን/ት የሚመለከት ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ልመለስ። አልሰማችሁ እንደሆን በኢትዮጲያዊያን መካከል በዓለም ደረጃ እርስበርሳችን መተባበርና መተሳሰብ ያለባቸው ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ እንቅስቃሴዎች ትጀምሯል ይባላል። ለምሳሌ - በአውሮፕ ደረጃ በአለፉት ዓመታት ስድስት የአውሮፓ ሀገሮች ውስጥ ያሉት ኢትዮጲያዊያን ተገናኝተው የስፖርት ውድድር አድርገዋል። የብዙ ሀገር ማዕከል በሆነችው በሆላንድ (አምስተርዳም) ነበር የተካሄደው። በዚህ ውድድር ግን ጣሊያን ያሉት ኢትዮጲያዊያን አልተሳተፉበትም። ቢሆንም እንደዚህ የመሳሰሉት አንዳንድ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ ነው ይባላል።
……....በዓለም ደረጃ ደግሞ በኅብረት ከአደረጉትና ካስፈጸሙት ሌላው ምሳሌ ሊሆን የሚችለው - ባህሬን (አረብ ሀገር) ያለችው የሺወርቅ ስው ገደለች መባሉ ሲሰማ ኢትዮጲያዊያን ድምፃቸውን አሰምተው ከሞት ቅጣት እንድትድን ተደረገች። አንዲት ኢትዮጲያዊ ሴት ሥራ ቀጣሪዋንና አሰሪዋን ሀብታም አረብ የሆነውን ግድያ ፈጸመች መባሉ እኔንም በጣም አስገርሞኛል። ይህችው እህታችን በኢትዮጲያ ዜግነቷ ሊያውም በሰው ሀገር የሞት ፍርድ ሲፈርድባት ሁላችንንም ውጪ ይለነውን ልባችንን ነክቶት ነበር። በሴትነቷ ላይ ብዙ በደል ተፈጽሞባትም ይባል ነበር። በተለይ በዋሺንግተን የነበረው የአበሻ ማኒፌስቶ ታይቶም አይታወቅም ነበር ይባላል። ባህሬን የነበረውም የኢትዮጲያ ኤምባሲ ይደረገው ጥረት የሚደነቅ ነበር ይባላል፡፡ ... ይቀጥላል ...
……....ሌላው ደግሞ በአውሮፓና በአሜሪካ መካከል በሚገኙ ኢትዮጲያዊያን በኢንተርኔት መገነኛ ተፈጥሮ አበሾች ብዙ ግልጋሎትን የሚሰጥ ሥራዎች እየሰሩ ነው ያሉት ይባላል። በአሜሪካ ትላልቅ ክተማዎችም ውስጥ ቅን አስተሳሰብ ባላቸው ኢትዮጲያውያን አንዳንድ ማዕከል መስርተው ለበርካታ ኢትዮጲያዊያን የነፃ ትምህርትን የሚያገኙበትን፣ በኢትዮጲያዊያን የሕግ ጠበቃዎች፣ በኢትዮጲያዊያን የኢንሽራንስ ኩባኒያ፣ በህመምም ሆነ በድንገት ኢትዮጲያዊ/ት በሞት ቢለይ ውዲያው በትንሽ ክፍያ በጊዜውና በቶሎ አስከሬኑ ተለቅሶለትና በክብር ሀገር ቤት የሚላክበትን መንገድ ሁሉ ፈጥረዋል። ልዩ የህክምና ግልጋሎት በቀለለ ወጪ እንዲያገኙና ሌላም አሁን ላስታውስ ያልቻልኩት ብዙ ችግሮቻቸውን የሚያቃልል ሁኔታዎችን አድርገዋል። ይህ እንግዴ በማህበራዊው ኑሮአቸው እድገት ሲያድርጉ ይታያል።
……....እናም በጣሊያን ሀገር የምንኖረው ኢትዮጲያዊያን በማናቸውም የዝቅተኛ ደረጃ ላይ መሆናችንን እንኳን መገንዘብ አቅቶናልና ህሊናችንን የማረጋጊያ መሠረት ለመጣል መሞከር ይገባናል። ... ይቀጥላል ... ...
……....እዚህም ፕሮጀክት ላላቸው ማኅበሮች ብዙ አይነት ድጋፍና እርዳታ እንደሚያገኙ ታውቃላችሁ? የገንዘብ፣ የማቴሪያልና የሰው ሀይል ለintegrazione በየ regione ይመድባሉ። ብዙ የውጪ ሀገር ክሚኒቲዎች ይህንን አጋጣሚ እንደሚጠቀሙበት ሰምቻለሁ። እኛም በሥራ ክፍፍል አድርገን አንዱ ላይ ብቻ የሥራ ሸክም እንዳይበዛበት ተራ በተራ በመተጋገዝ ቀጥ ብለን ብንሠራ ማድረግ እንችላለን። ዘፋኞችና ተወዛዋዦች ብቻ ጠርቶ ምሽት ማድረግ ብቻ ሳይሆን ፕሮጀክትና ፕሮግራሞችን በማዘግጀት የምፈጸሙ ሥራዎች አሉበት። የረቀቀ እቅድ እንድኖር ያስፈልጋል። እቅዱ ችግራችንን የሚቀርፍ፣ መንፈሳችንን የሚያፈካ፣ የስደተኛውን ስሜትና ፍላጎት ተንተርሶ የሚጓዝ መሆን አለበት። ከአለንበት አንድ እርምጃ ፈቀቅ የምንለው የስደተኛው ህልም ተከትሎ ሊሄድ የሚችል ማህበራዊ ፕሮግራም ሲኖረን ነው። እቅድ ወይም የፕሮጀክት ፕሮግራም ለማህበሮች ህልውና ተስፋና የማበብ ምልክት ነው። የማህበሮችን የአባላት በጎ ፈቃድና ተስትፎን ይጠይቃል። አቅጣጫውም እንዲያምር በህብረት መተጋገዝን ይጠይቃል። ... ይቀጥላል ...
……....ይህ አርዕስት ወደፊት ይቀጥላል።
*** *** *** *** ** *** *** *** *** *** *** *** *** *** *** *** *** *** *** *** *** *** *** ***
……....የዚህ ፅሁፍ ይዘት ምናልባት ብዙወቻችንን በቀጥታ ሊነካ ይችላል። አቤቱታ፣ ወቀሳና ትምህርት አለበት። ከልምድ አኳያ በብዙሃኑ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚታዩና የሚነገሩ ናቸው። ችግሮች የታወቁ እና ብዙዎቻችንን ይወክላሉ። እውን እንጂ ፈጠራ አይደለም። ለማህበራዊ ህይወታችን ብቻ ሳይሆን ለግል ህይወታችንም እንዲጠቅም ታስቦበታል።
……....* ልማዶቻችንንና ባህሪዎቻችንን በይፋ በማወጣት የሚበጁንን መፍትሄወችን ለማግኘት፣
……....* የልብ ውህደትና የአዕምሮ አንድነት እንዲኖረን ለማድርግ፣
……....* አዕምሯችንን ለተገቢው ነገር እንድንጠቀምበት መንገድ ለማሳየት፣
……....* ከልዩነታችን ይልቅ ለአንድነትና ለደህንነታችን እንዲናተኩር ለማበረታታት፣
……....* ሃላፊነት ለሌላው ከሰጠን በኋላ ከመተባበር ወደኋላ ላለማለት፣
……....* ሃላፊነትን ክመውሰድ ላለመሸሽ፣
……....* የማሕበር ሕብረት ሥራ ወይም ትብብር ላይ ሳንገኝ ... ... ...
... ይቀጥላል ...
……....አንድ ጊዜ ሀገር ቤት ሄጄ ስመለስ ዘመድቼ ያሉኝን ምን እንደሆን ታውቃላችሁ።
"ኢትዮጲያውያን/ት በውጪው ዓለም ፍቅራችሁ ልዩ ነው ይባላል። እውነት ነው ወይ?" ብለው ሲጠይቁኝ
"አይደለም ሁሉም የተገላቢጦሽ ነው" ብያቸዋለሁ። ምክንያቱም እንደኔ ከሆነ በሌላው ክፍለ ዓለም ያሉት ሊታባበሩና ሊፋቀሩ ይችሉ ይሆናል እንጂ በጣሊያን እንደዚህ አለመሆኑን አውቀዋለሁ። "እንደውም ለምን እንደሆነ የማይገባኝ ነገር በአንዳንድ አጋጣሚ ማንንም በማናውቅበት ለላ የጣሊያን ከተሞች ሄደን በመንገድ ላይ ስንገናኝ አንገት ደፍተን ሰላምታን እንኳን ሳንለዋወጥ የምንተላለፍበትም ጊዜ አለ" ብዬ ለዘመዶቼ ነግሬአቸዋለሁ። የሚያስተሳስረን ነገር እንደሌለ አድርገን መተላለፉን እራሴን ስጠይቅ መልስም አላገኘሁለትም። ግን ለምን?
……....* ትኩረትን ውደ ሥራ ብቻ አድርገን ነው?
……....* ኑሮ ስለከበደን ነው?
……....* ስደተኛነታችን እንዳይታወቅብን ነው?
……....* የውጪ ሀገር ዜጎች በመብዛታቸው ያለመተማመን ተፈጠረ?
……....* የቤተሰብ ናፍቆት መብዛት ፀባያችንን እንዲለወጥ አደረገው?
……....* በአለመገናኘታችን ከሰው ጋር የመግባባት ችሎታችን ተቀነሰ?
……....* የፈረንጁ ባህል የኛን እየቀየረብን ነው?
……....* አለመረጋጋት፣አለመተማመን፣ መናናቅ፣ ቅራኔዎች፣ ወሬ፣ ጭንቀት፣ ውጥረት፣ መኮራረፍ፣ ሀሜት፣ በአጠቃላይ በምን እንደሆነ ሊገባኝ አልቻለም። ብችግርም ሆነ በደስታ ሊደራረሱ የሚገባቸው የአንድ እናት ሀገር ልጆች ይህ እንኳን ሲሳናቸው ማየት ጥሩ ስሜት አይሰጥም።
……....ሌላው ደግሞ ሮማ ውስጥ ከገጠሜዎቹ አንዱ "ተጠንቀቅ አበሻ ዝም ተብሎ በመንገድ ሰላም አይባልም" ያለኝም አጋጥሞኛል። ይሄን ማለቱ ስለገረመኝ እኔም ቀጠል በማድረግ "እኔና አንተ አብረን ከመሆናችን በፊት ተያይተንም አናውቅም እኮ! በሰላምታ ብቻ አይደለም እንዴ የተቀራረብነው? እና ለምንድነው አበሻን ሰላም የማይባለው?" ለሚለው ጥያቄዬ መልሱንም አላገኘለትም። ለወትሮው እኛ ኢትዮጲያውያን/ት የምንታወቅበት በላምታችን ነበር። ክመተላለፍ አልፎማነህ? ከዬት መጣህ? እንዴት ነህ? መባባሉ እየተቀረ ነው መሰለኝ። እኔ ለመጀመሪያ ጊዜ የጣሊያንን ምድር ስረግጥ በእርግጥ ቁጥራችን በጣም ጥቂት ነበር። የዛሬ ሃያ ዓመት ከማላውቀው ወገኔ ጋር መንገድ ላይ የተያየን እንደሆነ በርቀትም ሆነ በቅርበት ሰላምታ ስንለዋወጥ ለብዙ ዓመት አብረን አፈር ፈጭተን ያደግን እንመስል ነበር። ተቀራርበን ተጫውተን የስልክ ቁጥር መለዋወጡ ከተለያየን በኋላም መደዋወሉና የልባችንን አውግተን ቀጥዩን መገናኛ ቀጠሮ መውሰዱስ። የዛሬ 20 ዓመት ማታ ማታ ስንገናኝ አዲስ አበባ ሊያውም ቄራ ወይም መሀል አራዳ ያለን ይመስል ነበር። በዚያን ጊዜ እርስ በርሳቸው የሚደባደቡ የውጪ ዜጎችን ስናይ እንገረም ነበር። እነሱም የኛን መከባበርና ሥነስራዓት ሲያዩ መንፈሳዊ ቅናት ያድርባቸው ነበር። በአጠቃላይ እንደዛሬው ሳይሆን እኛ አካባቢ ሰላም ነበር። ... ይቀጥላል ...
……....ዛሬ ነገሩ የተገላቢጦሽ ሆኖ የሌሎች የውጪ ሀገር ዜጎች በተለይም አፍሪካዊያን የሀገሩን ልጅ ቀርቶ ማንኛውንም የአፍሪካ ተወላጅ በመንገድ ሲያዩ ሰላምታን ይሰጣሉ። እነዚህም ዜጎች ሁኔታዎችን ፈጥረው ከመገናኘት ሲቦዝኑ አይቼ አላውቅም።
…….... እነሱ በእናንተ ክሙኒቲ ውስጥ ምን እየሠራችሁ ነው? ሕብረት አላችሁ ወይ? ብለው ሲጠይቁኝ መልስ ለመስጠት ሁሉ ተስኖኛል። ልምንድነው በተግባርና በሕብረታቸው ሊበልጡን ይቻሉት? እኛ እንደነሱ መተባበር ያቃተን ምክንያቱ ምንድነው?
……....ታዲያ እኔም ልሳሳት እችላለሁ ግን የውጪው ፍቅራችን የውሸት ነው። እንደውም እዚህ የመተከዝ ባህሪ ይታይብናል። ብንስቅም የውሸት ነው። (እውነተኛ ሳቅ ያለው በሀገር ነው) በመካከላችን መተማመን ያለ አይመስለኝም። ብዙዎቻችን መጠያየቅና መተዛዘንን እየረሳነው መጥተናል። አንዳንዶቻችንም ተኮራርፈንና ተደፋፍጠን ያለን እንመስላለን። ፍቅር ብዙም የለንም። ብትተክዝ ምን ሆንክ? ብታዝን ምነው? የሚለው ባህላችን እየተዳከመና እየቀረ መጥቷል። "በማር በወተት ያሳደግሽኝ እምዬ ኢትዮጲያ" እያልን ማንጎራግር፣ ስለሀገርና ስለቤተሰብ ናፍቆት ማውራትና እዚህ ስላለንበት ችግር ማሰቡን ብቻ ተያይዘነዋል። ሆዳችንም መባብቱንና ማልቀሱን ተያይዞታል። ችግራችንን ከልብ የሚያዳምጠን፣ የሚያጽናናን፣ የሚያጫውተን እውነተኛ ጓደኛ ስለማናገኝና በፊት ቀርበውን የነበሩት ሁሉ በወሬና በቅራኔ ስለራቁን በቃ ተለያይተን እንኖራለን። እርስ በርስችንም በወሬ ወገን እየፈጠርን በሌላው ላይ የመፍረድ ባህል እየተማርን ነው። "እንዲህ ሆነዋል፣ እንዲህ ያደርጋሉ" ሲባልና ሲሰማ ሰውን ከሰው ጋር ከማቀያየም ሌላ ምንም ነገር እንደማይጠቅም ማወቅ ያስፈልጋል። መቃቃርን በመፍጠር መለያየትን የምንወድ ከሆነ፣ መጠረቅ ባህላችን እየሆነ ከመጣ፣ የማይሆን ወሬ ማውራት ሱስ እየሆነብን ከመጣ በዚሁ መራራቃችን እንቀጥላለን ማለት ነው። አንገታቸውን ደፍተው ቤተሰብን ለመርዳትም ሆነ ራሳቸውን ለመቻል እየሠሩ ያሉትን ወገኖች መደባለቁም ጥሩ አይሆንም። "አይዟችሁ በርቱ፣ ቀን ያልፋል" ማለት እንጂ! "ከምን ጋር የዋለ ምንትስ" እያሉ ጨዋውን መርገምና መዝለፍ አይገባም። አንዱም በሌላው የቂም ጣት በመቀሰር የሚገኝ ጠቀሜታ እንደሌለ ማወቅ አለብን። ... ይቀጥላል ...
.
……....አስተውላችሁ ከሆነ ወይንም ገጥሞችሁ ከሆነ ነጮች ከፊታችሁ ጥሩ ፈገግታ ያሳዩና ዞር እንደተባለ ፊታቸውን ቅጭም ያደርጉታል። አሁንማ ይህንን ልማድ የኛዎች ጉደኞችም እየለመዱ ነው:: የሆነ ወቅት የኢትዮጵያን ሬስቶራንት ውስጥ ከጎኔ የተቀመጡት ወጣቶች እይተሳሳቁ ራት ከበሉ በሁዋላ ከመካከላቸው አንደኛው ከፍዬ ልሂድ ብሎ ይነሳል። የተቀሩት ሁለት ወጣቶች በጭራሽ እኛ ከሞትን በሀላ አይነት ግርግር ሲያነሱ ልጁ በሉ እንግዲህ በሰላም እደሩ grazie ብላቸው ተሰናብቶ ይወጣል:: የልጁ እግር ከሬስቶራንቱ እንደወጣ ልጁን ያላሉት ነገር አልነበረም:: ይሄ ሆዳም ዝም ብሎ በልቶ ይወጣል እንዴ? ክፈል ብንለው እኮ ያለቅስ ነበር እያሉ ጨዋታቸውን ይቀጥላሉ:: ይህ ልጅ ማድረግ ሲፈልግ አታድርግ ብለውት በሁዋላ ላይ መነጫነጭ አኛን አይጠቅምም ነው:: ከንዲህ አይነት ጎደኛ ይሰውራችሁ!! አሜን... ይቀጥላል ...





ሐበሾች ሰላም አንባባልም


አብራሃም ዘውዴ


……....ይህንን ርእስ ሐበሾች ወደሚገኙበት መድረክ ማምጣቱ አስፈላጊ ሆኖ ስለታየኝ እዚሁ ገጽ ላይ አምጥቼዋለው:: ከዚህ በታች እንደምታዩት በዚህ አርዕስት ላይ የተለያዩ ግለሰቦች አስተያየቶቻቸውን አስፍረዋል። የአንዱ አስተያየት ከሌላው ምን ያህል የተለየ መሆኑንም እንድንገነዘብ ያደርገናል። እስቲ እርስዎም በሰላምታ ጉዳይ የደረሰባችሁ ገጠመኝ ከአልዎት እዚሁ ይተንፍሱ:: ብዙዎቹ ለምን መንገድ ላይ ሰላም ሳይባባሉ ይተላለፋሉ? አርዕስቱን ሳትለቁ ያላችሁን አስተሳሰብ ወይም ሀሳባችሁን ስጡ:: መፍትሄ ካላችሁም አንድ በሉ። .
……....እኔ ያለሁበት ሀገር እንደታዘብኩት ሐበሻ በውስጡ የዘር ክፍፍል ጥርጣሬ ዋነኛው በሽታው ነው:: አንዳንዱ በየዋህነት ተንደርድሮ ሰላም ሲል ሌላው ደግሞ በአጸፋው የግልምጫ መልስ ስለሚያገኝ ሁለተኛ አይለመደኝም አፌ ይቆረጥ ይልና ሌላ ቀን ሀበሻ ሲያይ ይሸሻል:: ይህ እንግዴ እኔ ላይ የደረሰብኝ ቢሆንም እንኳን የፈለገው ይሁን እኔ በእድሜ ገፋ ያሉ ሐበሾች ወይም ግራ የተጋቡ የሚመስሉ ሀበሻም ይሁኑ ሌሎች አፍሪካዊያን የሚመስሉትን ሰዎች ሳይ አላልፍም:: ቆም ብዬ ተመልሼ በትህትና “ልርዳዎት ወዴት ነው የሚሄዱት?” እያልኩ መጠየቅ፤ በመንገድ ላይም እንኳን ባገኛቸው የመኪና ሊፍት መስጠት ልማዴ ነውና:: ታዲያ አንድ ቀን እንደ ልማዴ በአንዱ ባስ ፌርማታ ላይ በእድሜያቸው በግምት 50ዎቹ ውስጥ የሚገኙ ባልቴት የሀበሻ ነጠላና ጥበብ ቀሚስ አርገው ግራ የገባቸው መስለው ስላየሁኝ እንደ ልማዴ መኪናዬን አስጠግቼ ቆምኩና "እማዬ ሀበሻ ነዎት አይደል ላድርስዎት ወይ? የተቸግሩት ነገር አለ?" ብዬ ስጠይቃቸው ሰትዬዋ አይናቸው ድንገት ተለዋወጠና በተሰባበረ ጣሊያንኛ "ምንድ ነው የምታወራው" እያሉኝ በግልምጫ ጢሜን አበረሩት:: በጣም ግራ ተጋባሁኝ በአቅራቢያው የነበሩ ሌሎች ታዛቢዎች ተገርመው ሲያዩኝ ስለነበር ፖሊስ እንዳይጠሩብኝ ብዬ ተከናንቤ ወደ ቤቴ አመራሁኝ እላችኋለሁ:: ሌላ ቀን ደግሞ ለሥራ ጉዳይ ሌላ ከተማ ሄድኩኝና አንዷን ሀበሻ የሀበሻ ሬስቶራንት እንድትመራኝ ብጠይቃት አማርኛ እንደማይገባት ከግልምጫ ጋር ሬስቶራንቱ ያለበትን አላውቅም እንደማለት አይነት መልስ ሰጠችኝና አሁንም እያዘንኩና በአዕምሮዬ ብዙ ነገር እየተመላለሰ ሄድኩኝና ሌሎች ሰዎች የሚገኝበትን ቦታ አስረዱኝና ሄድኩ። ይሄኛው ገጠመኜ ደግሞ ለጉብኝት ካለሁበት ከተማ ወደ ሮማ የሄድኩ ቀን ላይ ነበር:: መቼስ በተወሰኑ የሮማ ሬስቶራንት ውስጥ በተለይ ረፋድ ማታ ላይ የሀበሻ ብዛት ታውቁታላችሁ:: ከብዛታቸው የተነሳ እንደ መርካቶ መተሻሸት እንጂ ለሰላምታ አይታሰብም:: እንደ እውነቱ ከሆነ ሮማ ውስጥ ሃበሻው በአጠገቤ አልፎ ሰላም አላለኝም ብሎ ማማረር ማለት የአዲስአበባ መርካቶ ውስጥ ሄደው ሁሉንም ሰው ሰላም በሉ እንደማለት ይቆጠራል:: ግን ከፍትፍቱ ፊቱ ይባላልና ቢያንስ አንዳችን ለአንዳችን ጥሩ ፈገግታ የማሳየት ባህል አለመደብንም:: ይሁንና ወደ አንዱ ሱቅ ጎራ አልኩኝና ሻጯ ሀበሻ መሆኗን ሳውቅ ሰላምታዬን አስቀደምኩኝና ከፍ ብሎ የተሰቀለውን ልብስ አውርዳልኝ እንዳየው ጠየኳት:: በጣም እንዳስጠላኋት እየታወቀባት በጣም በቀስታ እየተራመደች ዘንግ ስታነሳ የሱቁ ስልክ አንቃጨለ:: ዘንጉን እንደያዘች ስልኩን አነሳችና በአማርኛ የቤቷን ጉዳይ ዝክዝክ አርጋ ከፊቴ ማውራት ጀመረች:: ስሜቴን መቆጣጠር አቃተኝና እኔው ይቅርታ አልኳትና እንድታስተናግደኝ በምልክት ለመንኳት:: ጭራሽ ዘንጉን ሰጠችኝና አውርድ ብላኝ ተዝናንታ ወሬዋን ቀጠለች:: ዘንጉን ቁጭ አደረኩላትና ውልቅ አልኩኝ:: ሌላው የታዘብኩት ነገር ደግሞ ሀበሻ ሬስቶራንት ውስጥ የንድ አስተናጋጅ የምግብ ዝርዝር (ሜኑ) ትፈልጋለህ ወይስ የምትበላውን ታውቀዋለህ ብላ መጠየቋ ነው። ይህን የመሳሰሉትን ነገሮች ስናይ እንደገባኝ ሀበሾች እርስ በርሳቸው መሰላቻቸታቸውን በግልጽ ያሳያል። በርግጥ የመሸሹ ጉዳይ የዘር ክፍፍል ያመጣው በሽታ ነው ብዬ ራሴን ለማሳመን ብሞክርም የመሰለቻቸቱና የመናናቁ ጉዳይ ለምን ይሁን ብዬ ራሴን ብጠይቅ ምንም መልስ ያላገኘሁበት ሆኗል።

***


…….... ምንም ይሁን ከዚህ በፊት የማላውቀው ሰው መንገድ ላይ ሰላም አላለኝም ብዬ ሆዴን አይቆርጠኝም:: ነገርግን አንድ አከባቢ የምትኖር ከሆነ ትውውቅ እና ንጹህ መግባባት ቢኖር ለመረዳዳት ይጠቅማል:: የተቸገረን ሰው ወይም ርዳታ የሚያስፈልገው ሰው ከተቻለ ያለ ዘር እና ቀለም ማዳላት መርዳት ጥሩ ምግባር ይመስለኛል:: ከዚያ ውጪ መንገድ ላይ ያየሁትን ሰው አበሻ ይሆን? ሰላም ልበለው አልበለው? ምን አጨናነቀኝ:: ሀበሻ ከሌላው በምንም ዐይነት ልዩ የሚያደርገው ነገር እንደሌለው በብዙ ነገር ስላረጋገጥኩ ሰውን ሳላውቀው ማንንም ሰላም አልልም:: የማታውቀውን ሰው ገና ለገና ሀበሻ ነው ብሎ ሰላም ማለት የዋህነት ነው:: ድሮ ድሮ ሀበሻ የሚመስለውን ሁሉ ሳልረዳና ሳልጠይቅ እንዲሁም በአይኔ ሳልጠቅስ የማልፍበት ጊዜ አልነበረም:: ኋላ ኋላ ግን ለማላውቀው ሀበሻ ለሰአምታ መጨነቅ ካቆምኩ ዘመን አስቆጥርያለሁኝ:: ድሮ ድሮ ሀበሻ ሁሉ የእናቴ ልጅ ይመስለኝ ነበር:: አሁን ግን ተንኮለኛ ሀበሻ ብቅ ብቅ እያለ በሚያሳፍር ዜና በየጋዜጣው ፊት ገጽ ላይ ገጭ እያለ ነው:: የዘር ጥላቻ አዕምሮውን ያቆሸሸው ሀበሻም ስለበዛ::

***


……....አንድ ሰው ካገሩ ርቆ በባዕድ አገር ሲኖር ባይተዋርነት እንደሚሰማው ግልጽ ስለሆነና ይህን ለማስታገስ ያገር ልጆች በባዕድ አገር ሲገናኙ ሠላምታ መለዋወጥ ብርቅዬ ነው:: ኧረ ወግም ነው:: ሰዉ ባገሩ ምሉዕ ነው:: የስደት ኑሮ ግን ሁሌም ጉድለት አለው:: በስደት አለም ከሚኖሩ አፍሪካውያን ከሀበሻ በስተቀር አብዛኛዎቹ ይፈላለጋሉ፣ ይጠያየቃሉ፣ ከሩቅ በፉጨት ተጠራርተው ነው ሰላምታ የሚለዋወጡት:: እኔ ባለሁበት ሀበሻ ሳይ ተከትዬ ሠላም ብዬ አድራሻ ተለዋውጬ ነው የምለየው:: በምችለው ሁሉ ወጉን ጠብቄ አገራዊ ግዴታየን ለመወጣት እሞክራለሁ:: በተለይ ለአዲስ መጤ ሀበሻዎች በባዕድ አገር የአገር ልጅ ሰላምታ ለእነሱ ፈውስ ነው:: በእስካሁኑ ቆይታዬ የሸሸኝ ወይም የሸሸሁት የለም:: ይህን መሰል ምሬት ግን ከሌሎች ሰምቸዋለሁ:: "ሀበሻ በተፈጥሮ ድብቅ ነው:: ውስጡ እንዲታወቅበት አይሻም" ይህ ሽሽት ምናልባት አንዳችን የሌላውን ውስጥ ዘልቀን ለመፈተሽ ካለን ያለሳለሰ ጥረት ሊሆን ይችላል:: እያንዳንዱ ያለፈበት ሕይወት ራሱ አንድ ልቦለድ አይደል! ያ እንዲነበብበት አይፈልግ ይሆናል:: ሌላው ችግር ደግሞ ከሰላምታ ጋር ተያይዞ የሚመጣ ጨዋታ አለ:: የት ነው ምትኖረው? የት ነው ምትኖሪው? ስለ ስራ ሁኔታ መጠያየቅ አድራሻ መለዋወጥ መቀጣጥር:: መችም በባዕድ አገር ሁሉም ደስተኛ አይደለምና ጓደኝነትና ስራ የሚፈልግም ይኖራል:: ዜጋው ለዚህ ዝግጁ አይደለም:: ይህን ላለመስማት ሰላም አለማባባሉን ይመርጣል:: እኔ ሌላዉን ለመርዳት ወይም ለመጎዳኘት ካልፈለኩ በሠላምታ ብቻ ለመሸኘት ምንም አይቸግረኝም:: ልርዳ ካልኩም የሚያግደኝ የለም:: እኔ የማምነው ሞቅ ያለ ሠላምታም ራሱ እርዳታ ነው:: መተዋወቅም ጥቅም አለው:: ይህ ሁሉ የሚጀምረው ከሠላምታ ነው:: የዚህ አምድ ጥያቄ ከየዋህነት የመጣ ነው ካላችሁ እኔ አልስማማም:: ቶክዮ ወይም ለንደን ውስጥ አበሻ አይቼ ሠላም የማልልበት ምክንያት ጭንቀት እንጂ የዋህነት አይመስለኝም:: ምናልባት ጣሊያን የምንኖር ስሜታችንን እንደተረዳሁት ከረጅሙ አመታት ኑሮ በኋላ የሚመጣ የጣሊያዊነት ስሜት ይኖረናል። ይህ ስሜት ሀበሻነትን ሳናስበው ከውስጣችን ውስጥ እያሟሟ ይሄድና መንገድ ላይ ሰላምታ መለዋወጡ እውነትም እብደት ያስብላል:: ሐበሻዊነት ወኔና ስሜት እስካለን ድረስ እንዲሁም በባዕድ አገር እስከኖርን ድረስ ግን ሠላምታ መለዋወጡ ልዩ ምልክታችን ነውና አትዘንጉን አትዝጉን::

***


……....ስሜን ይጠይቀኛል፣ ከዛም ቁጥሬን ይጠይቀኛል ብሎ ሰላምታ አለመስጠት ደግሞ! በራስ የመተማመን ክፉኛ በሽታ ያለበት ነው:: ማንኛውም በሰላምታ ምክንያት ክሰ እንደማይደርስባቸው በአውራ ጣቴ እፈርምላቸዋለሁ:: እኔ አበሻን ሰላም እማልለው በበኩሌ አገር ቤት ብቻ ነው:: እሱን እማላደርገው ከህዝቡ ቁጥር አንጻር እያንዳንዱን ሰላም እያልኩ ለማለፍ ጊዜ ስለማይኖረኝ ነው:: ከዛ ውጪ አይተህን ሰላም ሳትለን አለፍክ እምትሉ ካላችሁ መካከለኛ ይቅርታ ጠይቄ የገንዘብ ካሳ እክፍላለሁ። ሀበሻ ስለሆኑ ብቻ ሰላም የምልበት ወይም ደግሞ ሀበሻ ስለሆኑ ፊቴን የማጠቁርበት ምክንያት የለም:: ከሰው ጋር አይን ላይን ከተገጣጠምኩኝ sorrido... non mi importa che persona è.

***


……....ለምን ሀበሻ ሰላም አላለኝም ብዬ ጠይቄም አላውቅም:: የማላቀው ሰው ሀበሻ ስለሆንኩ ብሎ ሰላም እንዲለኝ አልጠብቅም እኔም አልልም:: ይህ ጉዳይ ለምን እንደሚነሳ እራሱ አይገባኝም:: ይልቅ I would like to know ለምን ሀበሻ ሀበሻን ሲያይ ፊቱን እንደሚከሰክስ ነገርግን እንደዚህ ለማለት የቻልኩበት ገጠመኝ አለኝ:: ሁሌም ወደስራ ሳልፍ ቡና ገዝቼ የማልፍበት ቦታ አለ:: አንዲት ሀበሻ ልጅ ነበረች:: Barista ነች:: ከፊቴ ያሉትን በጥሩ ሁኔታ እያስተናገደች ነበር era il mio turno... Ho visto di come la sua faccia era cambiata... era ovvio che non era felice di vedere me tra la gente... ሌላ ግዜ ደግሞ ከፊት ለፊቴ የምትመጣ ልጅ ከኔ ጋር ከመተላለፍ በቀር ምንም አማራጭ አልነበራትም:: ልክ አጠገቤ ስትደርስ ፊቷን ክስክስ አድርጋ ስልኳን ማውራት ጀመረች (ስልኩ ጠርቶም አይመስለኝ):: በሰላም አገር እራስን ማጨናነቅ እስኪ ምን ይባላል። ሰላም አለማለት ባይኖር almeno በsorriso ማለፍ ሲቻል የማይሆን መጨናነቅና መኮሳተር እንዲሁም መሸሽን ምን አመጣው? ጎመን በጤና! እንዲያ በሩቁ ይሻላል።

***


……....ምኑ እንዳይቀርብኝ ነው ደግሞ ሰላም የምለው? ሴቷ ጫማ ጫማሽን ታያለች ወንዱ ደግሞ ፈገግ ካልሺለት ስምሽ ማነው ይላል? ስምሽን ከነገርሽው ደግሞ ስልክሽን አምጪ ይላል ወይ ስራሽን ያባትሽን ስም ዕድሜሽን ባንድ ቀን አጣርቶ መሄድ ይፈልጋል እንዲያው ልብ አውልቆች ናቸው:: ስለዚህ ሀበሻ ነሽ ብሎ የሚጠይቀኝ ሀበሻ በቀላሉ "አይደለሁም" ብዬ እገጨዋለሁ 2ኛ ቀና ብሎ ፊቴን አያያትም መንገድ እያቆራረጠ ሲፈረጥጥ እያየ....







እዚህ እስከኖሩ ድረስ ቋንቋውን ይወቁ።


ምክር ብጤ


……....ቋንቋ የተፈጠረው ለመግባባት፣ ያሰቡትንና የሚፈልጉትን ነገር በትክክል ለመግለፅ ነው፡፡ በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ ለመግባባት ወሳኝ የሆነና የብዙ ነገር መክፈቻ/መዝጊያ ዋናው ቁልፍ ነው ማለት ይቻላል። ቋንቋ በአንድነት ለመኖርና አንድ ቤተ ሰብ ለመሆን የመዋሃሃድ ቍልፍ ነው። እርስዎም በዚህ ማኅበረሰብ ውስጥ ንዋሪ እስከሆኑ ድረስ የማህበረሰቡን ቋንቋ ማወቁ ተገቢ ነው። የቋንቋ እድገት የዜጋን እድገት ከሚያመለክቱት ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ማወቁ በራሳችን እንድተማመን ያደርገናል፡፡ ማወቁ አንዱ የማደጋችን ምልክት ነው፡፡ ካላወቅንበት ግን ማደግ አንችልም፡፡ ከጎደለን ማንነታችንም አብሮ ይጎድላልና!! የምንፈልገውንና የሚሰማንን ነገር ለማስረዳት ከቸገረን ወይም የሚነግሩን ነገር ካልገባን በሀገሪቱ ማህበራዊ ኑሮአችን እንዲሁም በስራው ዓለም ጋር ከተያያዘው ሁኔታዎች ጋር አንድ ላይ መጓዝ ይቸግረናል፡፡ ሃሳብን ያለምንም በትክክል መግለፅ መቻል ማለት እራሱን የቻለ ጥበብ ነው፡፡ እውቀትና ኩራትም ነው፡፡ ለአንድ ማኅበረሰብ ባህል የሚያመጣው ተጽዕኖ ከፍተኛ ቦታ ስለሚይዝ ለማወቅ መጣርና መናገር ማለት ለሚያስተናግደን ማኅበረሰብም ክብር መስጠት እንደማለት ነው፡፡ ምክንያቱም የአንድ ማህበረሰብ ማንነቱን፣ እሴቱንና ባህሉን የሚጠብቅበት ቁልፍ ስለሆነ ነው። የሌላ ማኅበረሰብን ቋንቋ ለመረዳት መሞከር ማለት የማኅበረሰቡንም ባህል፣ ኑሮ፣ ዘይቤ፣ ... ለመረዳት ጥረት እንደማድረግ ሊቆጠር ይችላል።

……....ነገሮችን ካለመረዳት ወይም ካለማስረዳት መቀያየም፣ መጣላት፣ አለመግባባት ሊኖር ይችላል፡፡ ምናልባት በቋንቋው እጥረት ምክንያት ሊሆን ይችላል ግጭት የሚፈጠረው፡፡ የቋንቋን ጠቃሚነት ባለማስተዋል እራሳችንን ምን ያህል ራሳችንን እንጎዳለን፡፡ ቋንቋውን መናገር ብቻ ሳይሆን ብዙዎቻችን መፃፉንም በቅጡ አንችልበትም፡፡

……....የውጭ ቋንቋ ለእውቀትም ሆነ የውጭ ንባባትን ለማዳበር ጠቃሚነቱ አይካድም። ቢሆንም ለሀገራችንም ቋንቋዎች ትኩረት መስጠት ይገባል። ሀገራቸውን በቅጡ ለማያውቁት በባዕድ ሀገራት ለተወለዱ ልጆቻችን የራሳችንንም ቋንቋ ማቀበል ይገባናል። ዛሬ ሁላችንም እንደምንረዳው በሰው ሃገር ላይ ቁጥራችን በእጅጉ እየበዛ መጥቷል። የተለያዩ እንቡጦችንም እያፈራን ነው። ለነዚህ እንቡጦች ዘር፣ ኃይማኖት፣ ፖለቲካ፣ ሳይባል ብዙ ቁም ነገሮችን እየቀሰሙ ስለ ቋንቋቸውን ብቻ ሳይሆን መጸረት የሆነውን ባህላቸውን፣ ሃገራቸውን፣ የዘር ግንዳቸውን እንዲሁም ዕውቀት የሚያገኙበትና እርስ በርስ እየተማማሩ ከራሳቸው አልፈው ዜጎቻቸውንና ሃገራቸውን የሚጠቅሙ ትውልዶችን ለማፍራት መሰረት እንኳን ጥለንላቸው ብናልፍ ልጆቻችንን ለፍሬ ማብቃት ይቻላል:: አንድን ተክል ከመሰረቱ ጀምረን እየኮተኮትን አስፈላጊውን ማዳበሪያና ውሃ እያደረግን ስናሳድገው ሊጣመም ይችላል። በወቅቱና በሰዓቱ በችንካርም ቢሆን ካልመለስነው እንደተጣመመ ይቀርና በኋላ ለመመለስ ያስቸግራል። ልመልስህም ቢባል ይሰበራል እንጂ አይመለስም። ጠማማ ተክል ሁልጊዜ መጨረሻው ለአበባም ለፍሬም ሳይታደል ያለጊዜው ተቆርጦ ይቀራል።







የኛ ሰው በጣሊያን



አብራሃም ዘውዴ


……....በጣሊያን ወደ ሃያ አምስት ሺ የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ይኖራሉ። ከነዚህም መካከል ብዙዎቹ በርዕሰ ከተማይቱ ሮማ እና ሚላኖ ነው የሚገኙት። ለትምህርት ወደዚህ የመጡት እጅግ በጣም ጥቂት ሲሆኑ አብዛኞቹ ግን በተለያየው የጦርነት ክስተት፣ የፖለቲካ አመለካከት፣ አህጉራዊና ቤተሰባዊ ችግር የተነሣ የተሰደዱ ኛቸው።

……....ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ ከመጡት ውስጥ ደግሞ በረሃንና ባህርን አቋርጠው ብዙ ችግር ገጥሟቸው የገቡ ይገኙበታል። ከእነዚህም መሀከል በፍልሰት ላይ እያሉ ሕይወታቸውን ያጡትን ቁጥር ለማወቅ አዳጋች ነው። ታዲያ በመጡበት በመጀመሪያው ዓመታት ውስጥ በዶኩመንት፣ በኢንተግራዚዮኔ፣ በቋንቋና በኑሮዋቸው ላይ ችግር ያጋጥማቸዋል። እንደዚህ አይነት ችግሮቻቸውን ለማቃለል ወይም የሚረዳዱበትን መንገድ በመፍጠር እዚሁ በሚገኙ ወገኖች በአንዳንድ የጣሊያን ከተሞች ውስጥ ማኅበራት አቋቁመዋል። እነዚሁ ዜጎች ከአቋቋሙዋቸው ማኅበራት ውስጥ ...

……....1- የመረዳጃ ማህበር በማለት ለችግረኞች አስፈላጊ የሆኑትን ነግሮች ለምሳሌ ከድርጅቶችና ከመንግሥት መጠለያ፣ ምግብ፣ ... ወዘተ ... ለሟሟላት ይጥራሉ።

……....2- ወደተለያዩ በጎአድራጎት የሚያደርጉና ወደ የክፍለሀገሩ የውጪ ዜጎች እርዳታ ሰጪ ጽህፈት ቤቶች ... ወይም ወደ ካሪታስ እየተመሩ እንዲገለገሉ ያደርጋሉ።

……....3- ህግና ደንብ ባለው ማህበራቸውና በመንግስት በኩል ህልውና በተሰጠው ድርጅታቸው አማካይነት እርዳታዎችን እንዲያገኙ በማድርግ ጊዜያዊው ችግረኛ ወገናቸውን እስከሚቋቋም ድረስ ይደጉማሉ።

……....4- የጤና ህውከት ለሚኖራቸው ደግሞ ሙሉ የህክምና አገልግሎት እንዲሰጣቸው ... ... ...
5- ... ይቀጥላል ...

……....እዚህ ከሚኖሩት ወገኖች መካከል ከማንም ጋር ግኑኝነት የማያደርጉ፣ የተገለሉ፣ ያልታወቁ፣ የኑሮውን ውጣና ውረድ መቋቋም ያቃታቸው፣ የብቸኝነት ስሜት ያላቸው፣ የህሊና ዕረፍት የማያደርጉ፣ ለራሳቸው የሚሆን መዝናኛ ነገሮችን እንኳን የማያደርጉ የሀገር ልጆች ብዙ ናቸው። በመንፈስ ጭንቀት ወይም በአዕምሮ ህመም ምክንያት ብቻ ሊሠሩ ባለመቻላቸው ወደሀገር ቤት የሚመለሱም አይጠፉም። ለዚህም እንኳን የሥነ አዕምሮና የሥነ ልቦና ምክር ሊሰጥበት የሚችልበትን ማዕከል ለማግኘት የሚጠየቅበትን ሳያውቁ፣ የሚፈለገውን አገልግሎትና ህክምና ሳያገኙ ወደ ቤተሰባቸው የሚመለሱና የሚላኩ ጥቂቶች አይደሉም። ... ይቀጥላል ...

……....ጣሊያን በሙያ የሠለጠኑና በቀለም ትምህርት የገፉ ስደተኞችን የምታስተናግድ ሀገር ናት። ይሁንና በጣሊያን የውጭ ሀገር ስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽንና የአንዳንድ የውጪ ሀገር ተወላጅ ኮሙኒቲዎች የትብብር ጥናት እንደሚጠቁመው ይኸው እኛኑ የሚያስተናግደን ሀገር ስለስደተኞች የሙያ ችሎታ ተመክሮ አላደረገም። አድርጎም አያውቅም። እዚህ ጣሊያን ከሚገኙት በግምት ቁጥራችን ከ20ሺ እስከ 25ሺ የምንደርሰው ኢትዮጲያውያን ነዋሪዎች፣ ስደተኞችና ተገን ጠያቂዎች መካከል 70 በመቶ የምንሆነው መደበኛ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታችንን ያጠናቀቅን ነን። ከሀገር ከመኮብለላችን በፊት ብዙዎቻችን በልዩ ልዩ የሙያ ዘርፎች ተሰማርተን የተለያዩ የሥራ ልምዶች ያለንም አለን። ታዲያ የጣሊያን መንግሥት ይህንን ጉዳይ በሚመለከት አልመከረበትም፣ ችሎታቸንንም አልተጠቀመበትም። ከሌሎችም የውጪ ዜጎች መካከል በየሀገራቸው የዩንቨርስቲ ምሩቃን የሆኑና በሙያቸው የሰለጠኑትን ሁሉ ዕድሉ ቢሰጣቸው ለጣሊያን ብልፅግና የበኩላቸውን አስተዋጽዖ ማበርከት አይሳናቸውም። ... ይቀጥላል ...

……....ጥናቱ እንደሚያመለክተው እስከ 2005 አጋማሽ ድረስ 25% የሚደርሰው ስደተኛ በሥራው regolare ያልሆነ ነው። ማለትም እዚህ ከሚገኙት እስከ 4 ሚሊዮን ከሚደርሱት የውጪ ሀገር ዜጎች 500 ሺ የሚሆነው clandestini ነው ተብሎ ይገመታል። ሌላው ይህንኑ የሚያክለው ደግሞ ዶኩሜንት ወይም የመኖሪያ ፈቃድ ቢኖረውም ምንም ዓይነት ሥራ ወይም ገቢ የሌለው ነው። አብዛኞቹ ለህልውናቸው ሲጨነቁ ሲጠበቡ ነው የሚታዩት።
እንደዛም ሆኖ በእዚህ በተጠለልንበት ሀገር ውስጥ የውጪ ዜጋዎች ለሆንን ደህንነታችን የቱን ያህል አስተማማኝ ነው? ዓለማቀፍ መብታችንና ስበዓዊ ክብራችን የቱን ያህል ይጠበቃል? ወዘተ...
ታዲያ በዚሁ የውጪ ሀገር የኑሮ ችግርና የአጠቃላዩን የእኛን ስደተኞች ኑሮ እራሳችንንም እንኳ ለመገንዘብ እንዲያስችለን እስቲ ለመጀመሪያ ጊዜ እኛው ራሳችን መርምረን እንየው።

……....እንደሚታወቀው ለውጭ ዜጎች ፍልሰት መመሪያ ሰጪው ህግ ለብዙ ዓመታት ያህል ሲያከራክር ቆይቶ ነበር። ከውጭ ሀገር እየፈለሱ ወደ ጣሊያን ለሚገቡ ሰዎች መመሪያ ሰጪ የሆነው ይህ ረቂቅ ህግ በተቃውሞ ፓርቲዎች እስካሁን የስምምነት እልባት አላገኙለትም ማለት ይቻላል። ስምምነት ላይ የማይደርሱበት ምክንያት ለምን ይሆን? የህጉን ረቂቅ አንቀጾች በጥሞና መርምረው በድምጽ ብልጫ ተደርጎበት ከተስማሙበት በኋላ በብሔራዊው የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት (parlamento) ፀድቋል። በተቃውሞ ፓርቲዎችም ባለመደገፉ በጣሊያን ኅብረተሰብ ዘንድ ሰፊ ተቀባይነት አገኘ ወይም አላገኘም ማለት ያዳግታል። ... ይቀጥላል ...

……....ይህም ሆኖ ግን ጣሊያን ሀገር ለሚኖሩ የውጭ ተወላጆች ...

……....* የወደፊት የኑሮ እቅዳቸውን ለማውጣትም ሆነ ለማስተካከል የሚረዳ መሆን አለበት።

……....* የሠለጠነ የሰው ኃይል ምንጊዜም ተፈላጊነቱ ስላለ በከፍተኛ የጣሊያን የትምህርት ተቋማት የሚገኙ የውጭ ተወላጆች የሆኑ ተማሪዎች የተሻለ አማራጭ ዕድል ሊሰጣቸውና እኩል መብት እንዲኖራቸው ይገባል።

……....* የረጅም ጊዜ የመኖሪያ ፈቃድ ማግኘት የሚቻልበት ሁኔታም መቃለል አለበት።

……....* ለማንኛውም ሥራ ፈላጊ ለሆነው የውጪ ሀገር ተወላጅ በሩ ክፍት መሆን ይገባዋል።

……....* ተገን ጥያቂ ሰዎችን ካገር ማስወጣት ሳይሆን ዓለምአቀፋዊ የፖለቲካ ጥገኝነት መብት እንዳይነፈጋቸው መሆን ይገባዋል ... ይቀጥላል ...

……....ጣሊያን በኤኮኖሚና በህዝብ ቁጥር አለመመጣጠን ሳቢያ ለሚፈልሱት የውጭ ተወላጆች ቁጥር ምጨመር ምክንያት የምታስተናግድበት አቋም ወደፊት እንደነበረው አይሆንም። በጣሊያን ሀገር በአሁኑ ጊዜ 4 ሚልዮን የውጭ ዜጎች ይገኛሉ። የጣሊያን መንግሥት ለጋስነትን የሚያሳይበት እርምጃ ነው የተባለበት አንድ ሌላ ጉዳይ በአለፉት ዓምታት በጣሊያን ምድር ለሚገኙ የውጭ ተወላጆች ከህብረተሰቡ ጋር በማኅበራዊ ኑሮ መዋሀድ የሚችሉበትን መንገድ (integrazione) ለማቃናት ሲል በመንግስት ብዙ ሚሊያርድ ተመድቦ ወጪና ሰበካዎች ሁሉ አድርጎ ነበር። ለዚህም ማካሄጃ የሚሆነው ወጪ የተደረገው ስደተኛው እራሱ ከሚከፈለው የመመዝገቢያና የታክስ ገንዘብ ገቢ ወጪውን እንደሚሸፍንላቸው በማወቃቸው ነው። በዚህም ምክንያት የውጪ ዜጎችን ማስተናገድና በሥራ ማሰማራት ለኢኮኖሚያቸው እድገት ምን ያህል አስተዋጽዖ እንዳለው አምነውበታል። ይኼ ሁሉ ጥቅም እየተገኘበት እንዴት ለውጭ ዜጎች ፍልሰት መመሪያ የሚሰጠው አዲሱን ህግ እልባት አያገኙለትም?

……....ለምሳሌ ያህል ... ተገን ጥያቂዎችን ካገር ማስወጣት ሳይሆን ዓለምአቀፋዊ የፖለቲካ ጥገኝነት መብት እንዳይነፈጋቸው መሆን ይገባዋል። በእርግጥ በኒዮርክ፣ በዋሺንግተን፣ ለንደን እንዲሁም በማድሪድ አሸባሪዎች ጥፋት ካደረሱ ወዲህ ጣሊያን ውስጥ የፀጥታ ጉዳይ ይበልጥ እንዲታሰብበት አስገድዷል። ቀደም ሲል አክራሪ ሙስሊሞችን፣ በአሸባሪነት የሚጠረጠሩትና የተከለከሉ የድርጅቶች መሪዎችን፣ በሃይማኖትም ሆነ በጎሣ ላይ ያተኮረ ጥላቻን የሚሰብኩ ወንጀለኞችን ካገር ማባረራቸው ደግ ነው። ነገር ግን የህጉን አተረጓጎም ለውጦ ሁሉንም ተገን ጠያቂዎችን እንዳይነካ መሆን ይገባዋል። ... ይቀጥላል ...

……....ወደ አውሮጳው ኅብረት ስለስደተኞች ጉዳይ ስንመጣ ደግሞ ኅብረቱ ያቀደው የጋራው መመሪያ እስካሁን በሁሉም አባላት ሀገሮች አማካይነት አላገኘም ማለት ይቻላል። ምክንያቱም አባላቱ ሀገሮች የሚያስተላልፏቸው ሕግጋት አንደኛ በጽንሰ ሃሳብ የተለያዩ ናቸው። ለምሳሌ ስደተኞቹ የፖለቲካ ተገን በመጠየቅ ማመልከቻ ለሚያቀርቡት ሁኔታ አንዱ ከሌላው አውሮጳዊ ሀገር የተለያየ እርምጃ ነው የሚወሰደው። አለቅጥ አስቸጋሪ ሆኖባቸዋል።

…….... በታቀደው አዲስ መመሪያ ረገድ ከፍተኛ ቅሬታ እንዲኖር ከሚያደርጉት አንደኛው "የፖለቲካ ተገን ጠያቂ አቤቱታው ተቀባይነትን በሚያጣበት ጊዜ ወደ መጣበት ሀገር ይባረራል" የሚባልበት ሁኔታ ነው። ይህም ለተገን ጠያቂው ደህንነት አስተማማኝ ላይሆን ይችላል። ይባስ ተብሎ ተገን ጠያቂዎቹ ስደተኞች ወዲያው ከድንበር እንዲመለሱ የሚደረጉበት ሁኔታም ይገኛል። እንግዴህ ይህ ነጥብ የሚያመለክተው የኅብረቱ መመሪያ ምን ያህል ግልጽነት የተጓደለበት መሆኑን ነው። ስደተኞች ከድንበር እንዲመለሱ የሚደረግ ከሆነ በዚሁ ርምጃ አንፃር በተገን ጠያቂነታቸው መብት ላይ ይግባኝ የሚሉበት መብት ሁሉ ይጓደላል ማለት ነው።

…….... የፖለቲካ ተገን ጠያቂዎች ከሚያቀርቧቸው ማመልከቻዎች መካከል ከ5 በመቶ የሚደርሱቱ ብቻ ነው ድጎማና ትውቅናን የሚያገኙት። በዚህ አኳኋን እንግዲህ ከድንበር መባረር የሚፀና ከሆነ የፖለቲካ ተገን መብት ያላቸው ብዙ ስደተኞች የይግባኙ ሥርዓት ፍፃሜ ከማግኘቱ በፊት ሊባረሩ ይችላሉ ማለትም 95 በመቶ ወደሀገሩ በሚመለስበት ጊዜ ዋስትና ላይኖረው ይችላል ማለት ነው። የዓለሙ ድርጅት አሁን የሚሠጋበት በፖለቲካ ስደተኛነት ሳይሆን እንዲያው በፍልሰት ወደ አውሮጳ የሚሸጋገሩትን ወገኖች የሚመለከተው እምቢታ ወደ ስደተኞችም እየተዛወረ የውነተኛ ስደተኞች መብት የሚፋለስበትን ዝንባሌ መታየቱን ነው። በዚህም ምክንያት የአውሮጳው ኅብረት ከስደተኞች ጉዳይ መርሕ ጎንለጎን እውነተኛ የፍልሰት መርሕም እንዲኖረውና የእውነተኛ ስደተኛነትም ሁኔታ የሚጣራበት ቋሚ ሥርዓት እንዲፈጥር አስፈላጊ ሆኖ ነው የሚታየው። ... ይቀጥላል ...




የአበሻ ቀጠሮ

አብራሃም ዘውዴ

"የሰው ቀጠሮ ቀርጥፎ የሚበላ" ተብለን በፈረንጅ አፍ እንዳንገባና ትምህርት ይሆነን ዘንድ ስለቀጠሮ ማንሳቱ አስፈላጊ ነው። ይተገበራሉ የምንላቸውን ነገር በቀጠሮ የሚያዙ ስለሆኑ ስለቀጠሮ ትንሽ ቢባል የሚያስከፋ አይሆንም። ወይም የወደፊት እቅዳችን በቀጠሮዎች የሚያዝ ስለሆነ ሊፈፀም ይችል ዘንድ ቀጠሮን ማክበር ይገባል። ጥላሁን ገሠሠ በአንድ የሙዚቃ ካሴቱ ላይ...

"አርቆ ማሰቢያ እያለው አዕምሮ
ሰው እንዴት ይሳነው ለማክበር ቀጠሮ"

በማለት የነቀፈበትን ባለሁለት ስንኝ ግጥም መንደርደሪያ አድርገን ትንሽ እንበል። መቼም ስለቀጠሮ ሲነሳ ስለ “ጊዜ” መነሳቱ የማይቀር ነው። አዎ! "ጊዜ ወርቅ ነው" ተብሎ በሚነገርበት ሀገር እየኖርን ወይም ስለጊዜ ክቡርነት በሚነገርበት አገር እያለን በቀጠሮ አለመገኘትና ሰዓት አለማክበር ወይም ማርፈድ የኢትዮጵያዊነት ምልክት ተደርጐ መወሰዱ ለምን ይሆን? በቀጠሮ ሰዓት ያልተገኘ ኢትዮጲያዊ ሰው ሲገጥመን "ድሮስ አበሻ አይደል" እንላለን። እውነት “የአበሻ ቀጠሮ” የምንለው የተለመደው አባባል እኛን ኢትዮጵያዊያንን ለቀጠሮ ደንታ ቢስነት መሆናችንን ያሳያል? “የአበሻ ቀጠሮ” ይሚባለው መለያችን ሆኖ ሊቀር ነው እንዴ? አባቶቻችን...

"ከቶ አይቀርም ሞቱ ምንም ቢዋትቱ"
"አያሳስትም ሰዓት ቀጠሮ ያከብራል ሞት"

በማለት ቀጠሮ አክባሪው ሞት ነው ሲሉ የሞትን አይቀሬነት ገልፀዋል። ... ይቀጥላል ...


አበሻን መቅጠር እፈራለሁ!

……....አበሻን መቅጠር እፈራለሁ! ታዲያ "ያረፍድ ይሆን" ብዬ አይምሰላችሁ "ይመጣ ይሆን" ብዬ እንጂ፡፡
በቀጠሮ ጊዜ የሚያረፍድ አበሻ እራሱ ቀጥሮ ቢቀሩበት "ምንም አይደል" ብሎ መመለስ ጀምሯል። እያረፈድን "ይሁን" ማለት ተለመደ። የቀጠረን ሰው እየጠበቀን እያለ መቅረትም አለ፡፡ ታዲያ የአበሻ ቀጠሮን እንደ ቅርስ ልንጠብቅ እየከጀለን ወይም አሜን ብለን እየተቀበልነው ነው እኮ! ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻሉ እንደመምጣት በቀጠሮ ላይ የኛ ጉዳይ እንደ ግመል ሽንት ወደ ኋላ ሆኗል፡፡ ስለ ሌሎች አገሮች ባላውቅም እዚህ አካባቢ ግን ስላለው መናገር እችላለሁ፡፡

……....በቀጠሮ ላይ በሰዓቱና በቦታው የማይገኘውን ግለሰብ እንዴት እናየዋለን?
ብዙዎቻችን ዝርክርኮች ከመሆናችንም የተነሳ በቀጠሮ ጊዜ በቦታውና በሰዓቱ አንገኝም፡፡ በቀጠሮ የማይገኝ ወይም ያለበቂ ምክንያት የሚዘገይ ግለሰብ ከብጣሽ ወረቀት የበለጠ የቀለለ ግለሰብ ነው ማለት ይቻላል፡፡ በራሱ ብቻ ሳይሆን በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ዕቅድ የሌለውና ለራሱም ሆነ ለቀጠረው ግለሰብ ክብር የማያሳይ፣ የተዝረከረከና ሊተማመኑበት የማይችል አጉል ዜጋ ነው፡፡
……....ቀጠሮ ስለ አንድ ግለሰብ ማንነት ማወቂያና መገምገሚያ ትልቅ አጋጣሚ ነው፡፡ ብዙዎቹ ቁምነገርኛ፣ የሰለጠኑ፣ የሚከበሩ ሰዎች ቀጠሮን ያከብራሉ። ቁምነገረኛ የተባሉብትና የተከበሩበትም ሁኔታ አንዱ ቀጠሮን አክብረው በተዘዋዋሪም የቀጠሩትን ሰው በማክበራቸው የተነሳ ነው። የተማሩትም ቀጠሮ ያከብራሉ ስንል ብዙኃኑ ቁም ነገረኞች በመሆናቸውና ለቀጠሩት ሰው ክብር ስለሚሰጡ ነው። እናም ቀጠሮ ሻይ ለመጠጣት፣ ለመጨዋወት የመሳሰሉትን ለማድረግ የምንቀጣጠረውን ብቻ አይደለም፡፡ ለምሳሌ - ስብሰባ ሲኖር ቀጠሮ እንይዛለን፡፡ ዝግጅት ሲኖር በሰዓቱ ለመጀመርና ለመጨረስ ቀጠሮ እናደርጋለን፡፡ ታዲያ አዘጋጁም በወቅቱ ተዘጋጅቶና ተካፋዩም በሰዓቱ ተገኝቶ ጉዳዩን ለመፈፀም ሲያዳግታቸው ይታያል፡፡ አዘጋጆችም ከሆንን ቀደም ብለን አስበንበት ስለማንዘጋጅና ሃላፊነት ስለማይሰማን ጉዳዬችን በጊዜው አንፈጽመውም፡፡
……....ቀጠሮ ማድረግ ማለት በወቅቱ ለመገኘት ቃል መግባት ነው፡፡ ብዙዎቻችን ግን ቃላችንን እናፈርሳለን፡፡ ቃልን ማፍረስና ማጠፍ ደግሞ ወስላታና ውሸታም መሆን ማለት ነው፡፡ አውቀንም ሆነ ሳናውቅ ወስላታና ውሸታም መሆናችን አይሰማንም፡፡ ቢሰማንም ጎጂ መሆኑን በቅጡ አናስተውለውም፡፡ ምክንያቱም ቀጠሮን ያለማክበር ሁኔታ ስለተደጋገመ እንደ ልምድ ሆኖ እየቀረብን መጣ፡፡
……....በእርግጥ ቀጠሮን በተመለከተ ጥቂቶች እንሁን እንጂ ጠንቃቃ የሆንን አለን፡፡ የሚደንቀው ነገር ግን አንዳንዶቻችን በሰዓቱ ደርሰን የዘገዩትን ለምን ዘገየህ ብለን በምንጠይቅና በምንወቅስ ጊዜ ይባስ ብሎ ምን መልስ እንደሚሰጠን ታውቃላችሁ? "እባክህ አንተ ደግሞ ፈረንጂ አትሁንብን - ይሄ እኮ ያበሻ ቀጠሮ እኮ ነው!" መባላችን ነው፡፡ ወይም ደግሞ "ዝናብ ነበር"፣ "መጓጓዢያ አልነበረም" እንላለን፡፡ መቼም ሰነፍ ምክንያት አያጣም! እንደውም ለምን ሰዓቱን እንዳላከበረ ስትወቅሱት "ሰለጠንኩ ብለህ ነው ወይ?" ብለው አዙረው አንተን ጥፋተኛ አድርገው የሚመልሱም አይጠፉም፡፡ እንግዲህ ዋናው የብዙወቻችን ኢትዮጵያኖች ስህተት፣ በሰዓቱ መገኘት ማለት የፈረንጆች ባህል ብቻ መሆኑን ማመናችን ነው፡፡ ይህ የማስተዋልና የዕቅድ ማውጣት ጉዳይ እንጂ ሰዓት የማክበርን ባለቤትነት የወሰደ ዜጋ ወይም ዘር የለም፡፡ ይህ መታወቅ አለበት፡፡
……....ምክንያትን በመፍጠር በቀጠሮ ላይ በሰዓቱ አለመድረስ ወይም ሰዓቱን ባለማክበርና በዚሁ ስንፍናችን ከቀጠልን መደንቆር እንጂ አንሻሻልም፡፡ የምንኖረው ኢትዮጵያም ውስጥ ይሁን ውጭ አገር ሰው አደርጋለሁ ካለ ማድረግ አለበት፡፡ ቀጠሮ ከመያዛችን በፊት መቼና በምን ወደ ቀጠሮ ቦታ እንደሚኬድ እቅድ ማውጣት ያስፈልጋል፡፡ በቀጠሮውም ሰዓትና ቀን ሌላ ጉዳዮች እንደሌሉን ከበፊቱ ማወቅ አለብን። አብዛኛዎቻችን ኢትዮጵያዊያን በህይወታችን ውስጥ አንገብጋቢ የሆኑ ጉዳዮችን እንደ ተራ ነገር እንቆጥራቸዋለን፡፡ ከነዚህም ውስጥ አንዱ ቀጠሮን በተመለከተ ነው፡፡ ስለዚህ ከዚህ በታች እንደተጠቀሰው ብናደርግ እጅግ ይጠቅመናል፡፡

ቀጠሮን የሚያከብር ግለሰብ ...
……....ሀ) ለቀጠረው ግለሰብ ክብር ያሳያል፡፡
……....ለ) እራሱም ክብር እንደሚገባው በተግባር ያሳያል፡፡
……....ሐ) በተቃጠረው ጉዳይ ላይ ክብደት መስጠቱንና አስፈላጊነቱንም ያሳያል፡፡
……....መ) ጥንቁቅና ነገሮችን በዕቅድ የሚሰራ መሆኑን በተግባር ያሳያል፡፡ ስለዚህ በሚቀጥለው ጊዜ ቀጠሮ ሲኖረን የተጠቀሱትን ነጥቦች ብናስብባቸው አይከፋም፡፡ ... ይቀጥላል ...
ለምሳሌ ቀጠሮ በሰርግ ጥሪ ላይ...
በብዙ የሰርግ ጥሪ ወረቀቶች "ከቀኑ በ13.30 ሰዓት ላይ ለምሳ እንዲገኙልን" የሚሉ ግብዣዎች አሉ። ይባስ ብሎም "ቀጠሮ ያክብሩ" ወይም "በጊዜ እንዲገኙልን አደራ" የሚል ማሳሰብያ ጭምር ያዘለ ነው። ይሁንና በተባለው ሰዓት በቦታው ቢሄዱ ጭር ያለ ቦታ ነው። ሰርገኞቹ ሙሽሮቹን አጅበው ከሰዓት በኋላ በ15.00 ሰዓት ላይ “ጉሮ ወሸባዬ” እያሉ ወደ ዳስ ሲገቡ፣ ምሳ የሚቀርበው ወደ 16.00። ይህም ሁኔታ በጣሊያን ሀገር በምንገኘው ተደጋግሞ ይታያል። ቀጠሮ አክባሪነት በሃገራችን አጥብቆ እየተለመደ በመጣበት ዘመን፣ ጣሊያን ያለነው ምነው ቀጠሮ ማክበር ያቅተናል? መልሱ አጉል ልማድ… ነዋ! እራትማ ከሆነ ያው እኩለ ሌሊት መሆኑ ነው። እኩለሌሊት የሚቀርብ ከሆነ ደግሞ የጥሪውም ወረቀት ለእኩለ ሌሊት ተብሎ ይታረም። ካልሆነ ግን እራት ብሉ ተብሎ ጥሪ በተላከበት ሰዓት እራቱንም በወቅቱ ማቅረብ ይገባል። “ለ 20.00 ሰዓት እራት ድረሱ፣ አደራ” ብለው ሲያበቁ፣ እስከ እኩለ ሌሊት ሰውን አጉል ማስጠበቅና በረሃብ አለንጋ መግረፍ ተገቢ ነው ወይ?ይህ ሁኔታ ሊለወጥ ይገባዋል። እንግዲያውስ ለዛሬው እዚሁ ላቁም። ይህ የሁላችን ጉዳይ ስለሆነ ነው በአደባባይ ሹክ ያልኳችሁ፡፡ ሌሎች አንባቢዎች የሚሉትንና የሚጽፉትን ለመስማት እጠባበቃለሁ። መታረም ስላለባቸው ብቻ ሳይሆን መልካም ስለሆኑት ልማዶችም አሞጋግሶ መጻፉ ተገቢ ነው።
... ይቀጥላል ...


ዘመናዊ ትምህርት ለተሻለ የእድገት ደረጃ

ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ ጋር የተደረገ ቃለምልልስ

.......... የተወደዳችሁና የተከበራችሁ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር በመሆን ለምትከታተሉን ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች፣ ከሁሉ በፊት እንዴት ሰነበታችሁ? አብርሃም ዘውዴ እባላለሁ ከዚህ ድሕረ ገፅ አዘጋጆች አንዱ ነኝ::

.......... ባለፈው ጊዜ በቦሎኛ ዩኒቨርስቲና በአዲስ አበባ፣ በወለጋና በመቀሌ ዩኒቨርስቲዎች መካከል በጋራ ሊያሰራቸው የሚያስችል ሳይንሳዊ የቴክኖሎጂ ስምምነት መፈረሙን የሚያበስር ለሀገር የሚጠቅም ዜና ባጭሩ ለአንባቢያን ማቅረባችን ይታወሳል:: በጉዳዩ አስተያየቱን እንዲሰጠን ከፕሮጀክቱ አስተባባሪ ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ ጋር ያደረግኩትን ቃለምልልስ ከዚህ በመቀጠል አቀርብላችኋለሁ፣

.......... ጥያቄ፣ የቦሎኛን ዩኒቨርስቲ ከኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ጋር ማስተባበር ለምን አስፈለገ?
ዶ/ር ዘለቀ፣ የቦሎኛን ዩኒቨርስቲ ከአዲስ አበባ፣ ከወለጋና ከመቀሌ ዩኒቨርስቲዎች ጋር ማስተባበር አስፈላጊ የሆነበት ዋናው አብይ ምክንያት እንደምናውቀው በኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች በተለይም ዩኒቨርስቲዎች አብዛኞቹ ከተቋቋሙ ረጅም እድሜ የሌላቸው እንደመሆናቸው መጠን በቂ የትምህርት መሳሪያና ብቁ የሰለጠነ የሰው ሀይል ስለሚያንሳቸው ይህ ስምምነት ለተሻለ እድገት አቅጣጫና መንገድ ይቀይሳል የሚል እምነት ስላደረብኝ ነው::

.......... ጥያቄ፣ በጣሊያን ካሉት ሁሉ ዩኒቨርስቲዎች በተለይ የቦሎኛን ዩኒቨርስቲ እንዴት ልትመርጥ ቻልክ?
ዶ/ር ዘለቀ፣ በመጀመሪያ ደረጃ የቦሎኛ ዩኒቨርስቲ ከአውሮፓ አንጋፋው ዩኒቨርስቲ በመሆኑ በይዘቱና በጥራቱ የታወቀ ስለሆነና በዚሁ ዩኒቨርስቲ በትርፍ ጊዜዬ በማስተማር ሙያ ላይ ስለተሰማራሁ የቦሎኛን ዩኒቨርቲ ለመምረጥ ብዙ ጊዜም አልወስውደብኝም:: በሌላ በኩል ደግሞ አብረውኝ የሚሰሩት የድፓርትሜንት ሀላፊዎች በፕሮጀክቱ ተካፋይ መሆናቸውን በመግለፃቸውና በኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎችም በኩል ከፍተኛ ትብብር በማሳየታቸው ቦሎኛን መምረጥ ቻልኩ::

.......... ጥያቄ፣ ይህን ውጤት ለማግኘት ምን ያህል ጊዜ ወሰደባችሁ?
ዶ/ር ዘለቀ፣ በርግጥ ፊርማው ላይ ልንደርስ የቻልነው ከበርካታ ጥረቶች በኋላ ነው፣ በዚህ በጣሊያን በኩል ውሳኔ ላይ ከመድረስ በፊት አንዳንድ ጥቃቅን ውጣ ውረዶች ገጥመውን ነበር፣ ሆኖም ፕሮጀክቱ ተቀባይነት ይኖረዋል ተብሎ ስለታመነበት በትዕግሥት እስከመጨረሻው መከታተል አስፈላጊ በመሆኑ የሥራ ውጤቱ የሆነው ፊርማ ላይ ሊደረስ ተችሏል::

..........ጥያቄ፣ ስምምነቱ የተፈፀመው በዬትኛው የትምህርት መስክ ነበር?
ዶ/ር ዘለቀ፣ ስምምነቱ ለጊዜው የእርሻ፣ የሕግንና የታሪክ ትምህርቶችን ብቻ ይመለከታል::

.......... ጥያቄ፣ ለጊዜው ስትል በሌሎች ትምህርቶችስ ላይ የታሰበ ነገር አለ?
ዶ/ር ዘለቀ፣ ከነዚህ ስምምነቱ ከተደረሰባቸው የትምህርት ዘርፎች ሌላ በሚቀጥለው ዙር ደግሞ በሕክምናና በእንጅኔሪንግ ትምህርቶች ላይ ተመሳሳይ ሥራ በመሥራት ላይ እንገኛለን::

.......... ጥያቄ፣ በዚህ ፕሮጀክት በይበልጥ ተጠቃሚ የሚሆነው ማነው?
ዶ/ር ዘለቀ፣ በፕሮጀክቱ ተካፋይ የሆኑት ሁሉም ከላይ የጠቀስኳቸው ዩኒቨርስቲዎች ከፕሮጀክቱ ወደፊት ሊገኙ በሚችሉት ጥቅሞች ሁሉ በጋራ እኩል ተካፋይ ይሆናሉ:: አንዱ እርዳታ ለጋሽ ሌላው ገንዘብ ለማኝ የሆነበት አይነት ስምምነት አይደለም::

……....ጥያቄ፣ ለወደፊትስ በተመሳሳይ ተግባር እዚህ በመሆን ለኢትዮጵያ ምን የሥራ እቅድ አለህ?
ዶ/ር ዘለቀ፣ አዎን እኔ መደበኛ ሥራዬ ዩኒቨርስቲ ማስተማር ሳይሆን የሌላ ድርጅት ሰራተኛ ነኝ፣ እንደዚህ አይነቱን ተግባር የማከናውነው ካለኝ ትርፍ ጊዜ በመቆጠብ ነው፣ በኢትዮጵያ አንድ ጥሩ አባባል አለ “ከልብ ካለቀሱ እምባ አይገድም”:: አንድ ሰው አገሩን ለመርዳት ፍላጎቱ ካደረበት በተለያየ መልክ ሊረዳ ይችላል፣ እኔም ኢትዮጵያን በሙያዬ የመርዳት ግዴታ እንዳለብኝ በሚገባ ተረድቼ ይህንኑ ተግባራዊ በማድረግ ላይ እገኛለሁ:: በርግጥ ከሥራ መብዛት የተነሳ የተፈለገውን ያህል እንደሚታሰበው መሥራት አይቻልም አንዳንዴ የጊዜ ችግሮች ይገጥማሉ::

.......... ጥያቄ፣ በመጨረሻ ልታስተላልፍ የምትፈልገው መልእክት ካለህ?
ዶ/ር ዘለቀ፣ በኢትዮጵያ የዩኒቨርስቲዎችን ብዛት ብቻ ሳይሆን ጥራታቸውንም ጭምር መጠበቅ ከምንጊዜም በላይ አስፈላጊ በመሆኑ በውጭ ሀገር የምንኖር ኢትዮጵያዉያንም ሆንን የውጭ ሀገር ዜጎች ዘመናዊ ትምህርት ለተሻለ የእድገት ደረጃ በማለት ተገቢውን ሁሉ ማካሄድ ይኖርብናል እላለሁ ፣ አብርሃም አንተንም አመሰግንሃለሁ::
ደህና ሁኑ

Nessun commento: